unfoldingWord 21 - እግዚአብሔር መሲሑን ተስፋ ሰጠ

unfoldingWord 21 - እግዚአብሔር መሲሑን ተስፋ ሰጠ

Số kịch bản: 1221

ngôn ngữ: Amharic

Khán giả: General

Thể loại: Bible Stories & Teac

Mục đích: Evangelism; Teaching

Trích dẫn Kinh Thánh: Paraphrase

Trạng thái: Approved

Bản văn này là một hướng dẫn cơ bản cho dịch và thu âm trong các ngôn ngữ khác. Nó phải được thích nghi với nền văn hóa và ngôn ngữ để làm cho nó phù hợp với từng khu vực, nơi nó được sử dụng khác nhau. Một số thuật ngữ và khái niệm được sử dụng có thể cần một lời giải thích đầy đủ hơn hoặc thậm chí bị bỏ qua trong các nền văn hóa khác nhau.

Kịch bản

ገና ከመጀመሪያው፣ እግዚአብሔር መሲሑንለመላክ ዐቀደ። የመጀመሪያው የመሲሑ ተስፋ ወደ አዳምና ሔዋን መጣ። እግዚአብሔርየእባቡን ራስ የሚቀጠቅጥ የሔዋን ዘር እንደሚወለድ ተስፋ ሰጠ። ሔዋንን ያታለለው እባብ ሰይጣን ነበር። ተስፋው መሲሑ ሰይጣንን ፍጹም ያሸንፈዋል ማለት ነው።

በእርሱ በኩል የዓለም ሕዝብ ወገኖች በሙሉ በረከት እንደሚቀበሉ እግዚአብሔር ለአብርሃም ተስፋ ሰጠው። ይህ በረከት ወደ ፊት መሲሑ ሲመጣ ይፈጸማል። እርሱ በዓለም ካሉ ከሁሉም የሕዝብ ወገኖች የሆኑ ሕዝቦች እንዲድኑ ያደርጋል።

ወደ ፊት እንደ ሙሴ ያለ ሌላ ነቢይ እንደሚያስነሣ እግዚአብሔር ለሙሴ ተስፋ ሰጠው። ይህ ቆይቶ ስለሚመጣው መሲሕ የተሰጠ ሌላ ተስፋ ነበር።

ከዝርያዎቹ አንዱ በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ንጉሥ ሆኖ ለዘላለም እንደሚገዛ እግዚአብሔር ለንጉሥ ዳዊት ተስፋ ሰጠው። ይህም መሲሑ ከዳዊት ዝርያዎች አንዱ ይሆናል ማለት ነበር።

እግዚአብሔር ዐዲስ ቃል ኪዳን እንደሚያደርግ በነቢዩ ኤርምያስ በኩል ተስፋ ሰጠ፣ ይህ ቃል ኪዳን እግዚአብሔር በሲና ከእስራኤል ጋር እንዳደረገው ቃል ኪዳን ግን አይደለም። በዐዲሱ ቃል ኪዳን እግዚአብሔር ሕጉን በሕዝቡ ልብ ይጽፋል፣ ሕዝቡ በግል እግዚአብሔርን ያውቁታል፣ ሕዝቡ ይሆናሉ፣ እግዚአብሔር ኃጢአታቸውን ይቅር ይላል። መሲሑ ዐዲሱን ኪዳን ይጀምራል።

ደግሞም የእግዚአብሔር ነቢያት መሲሑ ነቢይ፣ ካህን እንዲሁም ንጉሥ ይሆናል አሉ። ነቢይ የእግዚአብሔርን ቃል የሚሰማ ከዚያም የእግዚአብሔርን ቃል ለሕዝቡ የሚያውጅ ሰው ነው። እግዚአብሔር ለመላክ ተስፋ የሰጠው መሲሕ ፍጹም ነቢይ ይሆናል።

እስራኤላውያን ካህናት ስለ ኃጢአታቸው በሚደርስባቸው ቅጣት ምትክ በሕዝቡ ፈንታ ለእግዚአብሔር መሥዋዕቶችን አቀረቡ። ደግሞም ካህናት ስለ ሕዝቡ ወደ እግዚአብሔር ጸለዩ። መሲሑ ፍጹም መሥዋዕት አድርጎ ራሱን ለእግዚአብሔር የሚያቀርብ ፍጹም ሊቀ ካህናት ይሆናል።

ንጉሥ በመንግሥቱ ላይ የሚገዛና በሕዝቡ ላይ የሚፈርድ ሰው ነው። መሲሑ በቅድማያቱ በዳዊት ዙፋን ላይ የሚቀመጥ ፍጹም ንጉሥ ይሆናል። በመላው ዓለም ላይ ለዘላለም ይገዛል፣ እንዲሁም ሁልጊዜ በቅንነት ይፈርድና ትክክለኛ ውሳኔ ይሰጣል።

የእግዚአብሔር ነቢያት ስለ መሲሑ ሌሎች ብዙ ነገሮችን ተንብየዋል። ነቢዩ ሚልክያስ መሲሑ ከመምጣቱ በፊት ታላቅ ነቢይ እንደሚመጣ አስቀድሞ ተነበየ። መሲሑ ከአንዲት ድንግል እንደሚወለድ ነቢዩ ኢሳይያስ ተነበየ። ነቢዩ ሚክያስ መሲሑ በቤተ ልሔም ከተማ ይወለዳል አለ።

ነቢዩ ኢሳይያስ መሲሑ በገሊላ ይኖራል፣ ልባቸው የተሰበረ ሰዎችን ያጽናናል፣ እንዲሁም ለተማረኩት ነጻነትንና ለታሰሩት መፈታትን ያውጃል። ደግሞም ነቢዩ መሲሑ የታመሙና መስማት፣ ማየት፣ መናገር፣ ወይም መራመድ የማይችሉትን ሕዝብ እንደሚፈውስ ተነበየ።

ደግሞም ነቢዩ ኢሳይያስ መሲሑ ያለ ምክንያት እንደሚጠላና ተቃውሞ እንደሚደርስበት ተነበየ። ሌሎች ነቢያት መሲሑን የገደሉት እነዚያ በልብሶቹ ላይ ዕጣ እንደሚጣጣሉና ወዳጁ እንደሚክደው አስቀድመው ተነበዩ። ነቢዩ ዘካርያስ መሲሑን ለሚክደው ወዳጅ ሠላሳ ብር እንደሚከፍሉት ተነበየ።

ደግሞም ነቢዩ ስለ መሲሑ አሟሟት ተናገረ። ኢሳይያስ ሰዎች መሲሑን እንደሚተፉበት፣ እንደሚያፌዙበትና እንደሚመቱት ተነበየ። ምንም ስሕተት ነገር ያላደረገ ቢሆንም እንኳ ይወጉታል በታላቅ ሕመምና ሥቃይ ይሞታል።

ደግሞም ነቢያት መሲሑ ኃጢአት የሌለበት ፍጹም ይሆናል አሉ። የሌሎች ሰዎችን ኃጢአት ቅጣት ለመቀበል እርሱ ሞተ። የእርሱ መቀጣት በእግዚአብሔርና በሰዎች መካከል ሰላምን ያመጣል። በዚህ ምክንያት መሲሑን ማድቀቅ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነበር።

መሲሑ እንደሚሞትና እግዚአብሔር ደግሞ ከሙታን እንደሚያስነሣው ነቢያት አስቀድመው ተነበዩ። እግዚአብሔር በመሲሑ ሞትና ትንሣኤ በኩል ኃጢአተኞችን ለማዳን ዕቅዱን ይፈጽምና ዐዲሱን ኪዳን ይጀምራል።

እግዚአብሔር ለነቢያት ስለ መሲሑ ብዙ ነገሮችን ገለጠላቸው፣ ነገር ግን መሲሑ ከእነዚያ ነቢያት በአንዳቸውም ጊዜ አልመጣም። ከእነዚህ ትንቢቶች የመጨረሻው ከተተነበየ ከ400 ዓመታት በኋላ፣ ልክ በትክክለኛው ጊዜ፣ እግዚአብሔር መሲሑን ወደ ዓለም ይልካል።

Thông tin liên quant

Lời Sự Sống - GRN có lưu trữ hàng ngàn thu âm của các lời dạy Phúc Âm bằng các thứ tiếng khác nhau bao gồm từ những thông điệp cơ bản từ Kinh thánh

Tài liệu miễn phí - Tại đây bạn có thể tìm thấy các thông điệp chính của GRN bằng các thứ tiếng khác nhau bao gổm cả hình ảnh và các tài liệu khác có liên quan có thể tải xuống được

Thư viện âm thanh của GRN - Các tài liệu giảng dạy Kinh Thánh cơ bản và nâng cao phù hợp với nhu cầu và văn hóa của mọi người, đa dạng về cả hình thức và phong cách

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?