unfoldingWord 06 - እግዚአብሔር ለይስሐቅ ሚስት አዘጋጀለት
개요: Genesis 24:1-25:26
스크립트 번호: 1206
언어: Amharic
청중: General
장르: Bible Stories & Teac
목적: Evangelism; Teaching
성경 인용: Paraphrase
지위: Approved
이 스크립트는 다른 언어로 번역 및 녹음을위한 기본 지침입니다. 그것은 그것이 사용되는 각 영역에 맞게 다른 문화와 언어로 조정되어야 합니다. 사용되는 몇 가지 용어와 개념은 다른 문화에서는 다듬어지거나 생략해야 할 수도 있습니다.
스크립트 텍스트
አብርሃም በጣም ባረጀ ጊዜ ይስሐቅ ዕድሜው ለአቅመ አዳም ደረሰ። ስለዚህ አብርሃም ከአገልጋዮቹ አንዱን ወደ ዘመዶቹ ምድር ለልጁ ለይስሐቅ ሚስት እንዲያመጣለት ላከው።
የአብርሃም ዘመዶች ወደሚኖሩበት ምድር ከረጅም ጒዞ በኋላ ደረሰ። እግዚአብሔርም የተላከውን የአብርሃምን አገልጋይ ወደ ርብቃ መራው። ርብቃ የአብርሃም ወንድም የልጅ ልጅ ነበረች።
ርብቃ ቤተ ሰቦቿን ትታ ከአገልጋዩ ጋር ወደ ይስሐቅ ቤት ለመሄድ ተስማማች። እንደ ደረሰችም ይስሐቅ አገባት።
ከረጅም ጊዜበኋላ አብርሃምሞተና እግዚአብሔርከአብርሃም ጋርየገባው የተስፋ ቃል ኪዳን ሁሉ ወደ ይስሐቅተላለፈ። እግዚአብሔርለአብርሃም ሊቈጠር የማይችል ዘር እንደሚኖረው ተስፋ ሰጥቶት ነበር። ይሁን እንጂ የይስሐቅ ሚስት ርብቃ ልጆች ልትወልድ አልቻለችም።
ይስሐቅ ለርብቃ ጸለየላትና እግዚአብሔር መንታ ልጆችን እንድታረግዝ ፍቃዱ ሆነ። ሁለቱ ልጆች በርብቃ ማኅፀን ሳሉ እርስ በርሳቸው ይታገሉ ነበር። ርብቃም በማኅፀንዋ እየሆነ ያለው ምን እንደሆነ እግዚአብሔርን ጠየቀች።
እግዚአብሔርም ርብቃን አላት፣ “በማኅፀንሽ ካሉት ከሁለቱ ልጆች ሁለት ሕዝቦች ይወጣሉ እነርሱም እርስ በርሳቸው ይታገላሉ ታላቁም ታናሹን ያገለግላል” አላት።
የርብቃ ልጆች በተወለዱ ጊዜ ታላቁ ልጅ ቀይና ፀጉራም ሆኖ ወጣ ‘ኤሳው’ ሲሉትም ስም አወጡለት፤ ታናሹም ልጅ የኤሳውን ተረከዝ ይዞ ወጣ ስሙንም ‘ያዕቆብ’ ሲሉ አወጡለት።