unfoldingWord 06 - እግዚአብሔር ለይስሐቅ ሚስት አዘጋጀለት
![unfoldingWord 06 - እግዚአብሔር ለይስሐቅ ሚስት አዘጋጀለት](https://static.globalrecordings.net/300x200/z01_Ge_25_01.jpg)
အကြမ်းဖော်ပြချက်: Genesis 24:1-25:26
ဇာတ်ညွှန်းနံပါတ်: 1206
ဘာသာစကား: Amharic
ပရိသတ်: General
အမျိုးအစား: Bible Stories & Teac
ရည်ရွယ်ချက်: Evangelism; Teaching
သမ္မာကျမ်းစာကိုးကားချက်: Paraphrase
အဆင့်အတန်း: Approved
ဇာတ်ညွှန်းများသည် အခြားဘာသာစကားများသို့ ပြန်ဆိုခြင်းနှင့် အသံသွင်းခြင်းအတွက် အခြေခံလမ်းညွှန်ချက်များ ဖြစ်သည်။ မတူကွဲပြားသောယဉ်ကျေးမှုနှင့် ဘာသာစကားတစ်ခုစီကို နားလည်မှုရှိစေနိုင်ရန်နှင့် ဆက်စပ်မှုရှိစေရန် ၎င်းတို့ကို လိုအပ်သည့်အတိုင်း ပြင်ဆင်သင့်သည်။ အသုံးပြုနေသည့် အချို့သောဝေါဟာရများနှင့်သဘောတရားများကို ပိုမို ရှင်းပြရန် လိုအပ်နိုင်သည်၊ သို့မဟုတ် အစားထိုးခြင်း သို့မဟုတ် လုံးလုံး ချန်လှပ်ထားနိုင်သည်။
ဇာတ်ညွှန်းစာသား
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z01_Ge_24_03.jpg)
አብርሃም በጣም ባረጀ ጊዜ ይስሐቅ ዕድሜው ለአቅመ አዳም ደረሰ። ስለዚህ አብርሃም ከአገልጋዮቹ አንዱን ወደ ዘመዶቹ ምድር ለልጁ ለይስሐቅ ሚስት እንዲያመጣለት ላከው።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z01_Ge_24_08.jpg)
የአብርሃም ዘመዶች ወደሚኖሩበት ምድር ከረጅም ጒዞ በኋላ ደረሰ። እግዚአብሔርም የተላከውን የአብርሃምን አገልጋይ ወደ ርብቃ መራው። ርብቃ የአብርሃም ወንድም የልጅ ልጅ ነበረች።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z01_Ge_24_11.jpg)
ርብቃ ቤተ ሰቦቿን ትታ ከአገልጋዩ ጋር ወደ ይስሐቅ ቤት ለመሄድ ተስማማች። እንደ ደረሰችም ይስሐቅ አገባት።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z01_Ge_25_01.jpg)
ከረጅም ጊዜበኋላ አብርሃምሞተና እግዚአብሔርከአብርሃም ጋርየገባው የተስፋ ቃል ኪዳን ሁሉ ወደ ይስሐቅተላለፈ። እግዚአብሔርለአብርሃም ሊቈጠር የማይችል ዘር እንደሚኖረው ተስፋ ሰጥቶት ነበር። ይሁን እንጂ የይስሐቅ ሚስት ርብቃ ልጆች ልትወልድ አልቻለችም።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z01_Ge_25_02.jpg)
ይስሐቅ ለርብቃ ጸለየላትና እግዚአብሔር መንታ ልጆችን እንድታረግዝ ፍቃዱ ሆነ። ሁለቱ ልጆች በርብቃ ማኅፀን ሳሉ እርስ በርሳቸው ይታገሉ ነበር። ርብቃም በማኅፀንዋ እየሆነ ያለው ምን እንደሆነ እግዚአብሔርን ጠየቀች።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z01_Ge_25_03.jpg)
እግዚአብሔርም ርብቃን አላት፣ “በማኅፀንሽ ካሉት ከሁለቱ ልጆች ሁለት ሕዝቦች ይወጣሉ እነርሱም እርስ በርሳቸው ይታገላሉ ታላቁም ታናሹን ያገለግላል” አላት።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z01_Ge_25_04.jpg)
የርብቃ ልጆች በተወለዱ ጊዜ ታላቁ ልጅ ቀይና ፀጉራም ሆኖ ወጣ ‘ኤሳው’ ሲሉትም ስም አወጡለት፤ ታናሹም ልጅ የኤሳውን ተረከዝ ይዞ ወጣ ስሙንም ‘ያዕቆብ’ ሲሉ አወጡለት።