unfoldingWord 27 - የደጉ ሳምራዊ ታሪክ

unfoldingWord 27 - የደጉ ሳምራዊ ታሪክ

Balangkas: Luke 10:25-37

Bilang ng Talata: 1227

Wika: Amharic

Tagapakinig: General

Klase: Bible Stories & Teac

Layunin: Evangelism; Teaching

Kawikaan mula sa Bibliya: Paraphrase

Katayuan: Approved

Ang mga script ay panimulang gabay para sa pagsasalin at pagre-record sa ibat-ibang wika.Ang mga ito ay ay dapat na angkupin kung kinakailangan para maunawaan at makabuluhan sa bawat kultura at wika. Ilang termino at konsepto na ginamit ay maaaring gamitin para maipaliwanag o maaari di na palitan o tanggalin ng ganap.

Salita ng Talata

አንድ ቀን አንድ የአይሁድ ሕግ ዐዋቂ ሊፈትነው ወደ ኢየሱስ መጣ፣ “መምህር ሆይ፣ የዘላለምን ሕይወት እንድወርስ ምን ላድርግ?” አለው። ኢየሱስ፣ “በእግዚአብሔር ሕግ የተጻፈው ምንድን ነው?” ብሎ መለሰለት።

ሕግ ዐዋቂው የእግዚአብሔርሕግ፣ “ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም ኃይልህም በፍጹም ዐሳብህም ውደድ። ባልንጀራህንም እንደ ራስህ ውደድ” ይላል ብሎ መለሰ። ኢየሱስ፣ “ትክክል ነህ! ይህን አድርግ በሕይወትም ትኖራለህ” አለው።

ነገር ግን ሕግ ዐዋቂው ጻድቅ መሆኑን ለማረጋገጥ ፈለገ፣ ስለዚህ፣ “ባልንጀራዬ ማን ነው?” ብሎ ጠየቀ።

ኢየሱስ ታሪክ በመናገር ለሕግ ዐዋቂው መለሰለት። “ከኢየሩሳሌም ወደ ኢያሪኮ ይጓዝ የነበረ አንድ አይሁዳዊ ነበረ።”

“ሰውዬው በመጓዝ ላይ እያለ ወንበዴዎች ያዙት። የነበረውን ነገር ሁሉ ወሰዱበትና እስኪሞት ድረስ ደበደቡት። ከዚያም ሄዱ።”

ከዚያ በኋላ ወዲያውኑ አንድ አይሁዳዊ ካህን በዚያ መንገድ ይጓዝ ነበር። ይህ የሃይማኖት መሪ የተዘረፈውንና የተደበደበውን ሰው ባየ ጊዜ ወደ መንገዱ ሌላኛ ጎን ሄደ፣ ርዳታ የፈለገውን ሰው ቸል አለውና ጕዞውን ቀጠለ።"

ከዚያ በኋላ ብዙም ሳይቆይ፣አንድ ሌዋዊ መጣ።( ሌዋውያን በቤተ መቅደስ ካህናቱን የሚረዱ የአይሁድ ነገድ ነበሩ።) ሌዋዊውም ደግሞ ወደ መንገዱ ሌላኛ ጎን ተሻገረና የተዘረፈውንና የተደበደበውን ሰው በቸልታ አለፈው።"

በዚያ መንገድ የወረደው የሚቀጥለው ሰው ሳምራዊ ነበር።(ሳምራውያን የሌሎች አገሮች ሰዎችን ያገቡ የአይሁድ ዝርያዎች ነበሩ።ሳምራውያንና አይሁዳውያን እርስ በርስ ይጠላሉ ነበር።) ነገር ግን ሳምራዊው አይሁዳዊውን ባየ ጊዜ በጣም አድርጎ ራራለት። ስለዚህ ተንከባከበውና ቊስሉን አሰረለት።"

“ከዚያ በኋላ ሳምራዊው ሰውዬውን አንሥቶ በራሱ አህያ ላይ አስቀምጦት ወደ እንግዶች ማደሪያ ወሰደው ተንከባከበውም።”

“በማግሥቱም ሳምራዊው ጕዞውን መቀጠል አስፈለገው። ለእንግዶች ማረፊያው ባለቤት ጥቂት ገንዘብ ሰጠውና፣”ተንከባከበው፣ ከዚህ ሌላ ገንዘብ የምታወጣ ከሆነ በምመለስበት ጊዜ እከፍልሃለሁ አለው።"

ከዚያ በኋላ ኢየሱስ ሕግ ዐዋቂውን፣ “ምን ታስባለህ? ለተዘረፈውና ለተደበደበው ሰው ባልንጀራው ከሦስቱ ሰዎች የትኛው ነበር?” ብሎ ጠየቀው። እርሱም፣ “ምሕረት ያደረገለት ነበር” ብሎ መለሰለት። ኢየሱስ፣ “አንተም ሄደህ እንደዚሁ አድርግ” ብሎ ነገረው።

Katulad na kaalaman

Salita ng Buhay - Ang GRN ay mayroong mensahe sa audio sa libo-libong wika na naglalaman ng mensahe base sa Bibliya tungkul sa kaligtasan at Kristyanong pamumuhay.

Libreng mga download - Dito ay matatagpuan ang lahat ng pangunahing scripts mensahe ng GRN sa ibat-ibang wika, at mga larawan at iba pang katulad na materyales, ay maaari ng i-download.

Ang GRN Aklatang Audio - Pag-eebanghelyo at panimulang kagamitan ng katuruang Bibliya na angkop sa mga pangangailangan at kultura ng mga tao sa isang iba't ibang estilo at mga format.

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?