unfoldingWord 43 - ቤተ ክርስቲያን ተጀመረች

unfoldingWord 43 - ቤተ ክርስቲያን ተጀመረች

เค้าโครง: Acts 1:12-14; 2

รหัสบทความ: 1243

ภาษา: Amharic

ผู้ฟัง: General

ประเภท: Bible Stories & Teac

เป้าหมายของสื่อบันทึกเสียง: Evangelism; Teaching

ข้ออ้างอิงจากพระคัมภีร์: Paraphrase

สถานะ: Approved

บทความเป็นแนวทางพื้นฐานสำหรับการแปลและบันทึกเสียงภาษาอื่นๆ ควรดัดแปลงตามความจำเป็นเพื่อให้เข้าใจและเหมาะสมกับวัฒนธรรมและภาษาแต่ละภาษา คำศัพท์และแนวคิดบางคำที่ใช้อาจต้องอธิบายเพิ่มเติม หรือแทนที่ หรือตัดออก

เนื้อหาบทความ

ኢየሱስ ወደ ሰማይ ከተመለሰ በኋላ፣ ደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስ እንዳዘዛቸው በኢየሩሳሌም ቆዩ። በዚያ የነበሩት አማኞች ለመጸለይ ያለ ማቋረጥ ተሰበሰቡ።

አይሁድ በያመቱ ከፋሲካ በኋላ ባሉት 50 ቀናት ጴንጤቆስጤ ተብሎ የሚጠራ አስፈላጊ ቀን ያከብሩ ነበር። ጴንጤቆስጤ አይሁድ የመከር በዓልን የሚያከብሩበት ቀን ነበር። አይሁድ ጴንጤቆስጤን በአንድነት ለማክበር ከመላው ዓለም ወደ ኢየሩሳሌም ይመጡ ነበር። በዚህ ዓመት፣ ኢየሱስ ወደ ሰማይ ከተመለሰ ከአንድ ሳምንት ገደማ በኋላ የጴንጤቆስጤ ጊዜ መጣ።

አማኞቹ ሁሉ በአንድነት ተሰብስበው እያሉ፣ በድንገት የነበሩበት ቤት ድምፅ በመሰለ ብርቱ ነፋስ ተሞላ። ከዚያም በአማኞቹ ሁሉ ራስ ላይ የእሳት ነበልባል የሚመስል ነገር ታየ። ሁላቸውም በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉና በሌሎች ቋንቋዎች መናገር ጀመሩ።

በኢየሩሳሌም የነበሩት ሰዎች ድምፅን በሰሙ ጊዜ፣ በመሆን ላይ የነበረውን ነገር ለማየት በብዛት መጡ። አማኞቹ የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራዎች ሲያውጁ ሰዎቹ በሰሙ ጊዜ እነዚህን ነገሮች በገዛ ራሳቸው ቋንቋ በመስማታቸው ተደነቁ።

አንዳንዶቹ ሰዎች ደቀ መዛሙርቱ ሰክረዋል ብለው ወቀሱአቸው። ነገር ግን ጴጥሮስ ቆመና እንዲህ አላቸው፣ “ስሙኝ! እነዚህ ሰዎች አልሰከሩም! እግዚአብሔር በነቢዩ ኢዮኤል ‘በመጨረሻው ቀን መንፈሴን አፈስሳለሁ!’ ያለው ትንቢት በዚህ ይፈጸማል።

“የእስራኤል ሰዎች ሆይ፣ እናንተ እንዳያችሁትና አስቀድማችሁ እንደምታውቁት ኢየሱስ በእግዚአብሔር ኃይል ብዙ ታላላቅ ምልክቶችንና ድንቆችን ያደረገ ሰው ነው። ነገር ግን እናንተ ሰቀላችሁት!”

“ኢየሱስ ቢሞትም እንኳ እግዚአብሔር ከሙታን አስነሣው። ይህም ‘ቅዱስህንም በመቃብር መበስበስን ያይ ዘንድ አትተወውም’ የሚለው ትንቢት ፍጻሜ ነው። እግዚአብሔር ኢየሱስን ሕያው አድርጎ እንዳስነሣው እኛ ምስክሮች ነን።”

“ኢየሱስ አሁን በእግዚአብሔር አብ ቀኝ ከፍ ብሎአል። ደግሞም ኢየሱስ ልክ ተስፋ እንደ ሰጠው መንፈስ ቅዱስን ልኮአል። አሁን የምታዩአቸውንና የምትሰሙአቸውን ነገሮች መንፈስ ቅዱስ ነው ያደረጋቸው።

“ይህንን ኢየሱስን ሰቀላችሁት። ነገር ግን እግዚአብሔር ኢየሱስን ጌታና መሲሕ እንዳደረገው በእርግጥ እወቁ!”

ጴጥሮስን ይሰሙ የነበሩት ሰዎች በተናገራቸው ነገሮች በእጅጉ ተነኩ። ስለዚህ ጴጥሮስንና ደቀ መዛሙርቱን፣ “ወንድሞች ሆይ፣ ምን እናድርግ?” ብለው ጠየቁአቸው።

ጴጥሮስ እንዲህ ብሎ መለሰላቸው፣ “እግዚአብሔር ኃጢአታችሁን ይቅር እንዲላችሁ እያንዳንዳችሁ ንስሐ ግቡና በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ። ከዚያ በኋላ እርሱ የመንፈስ ቅዱስን ስጦታ ደግሞ ይሰጣችኋል።”

3000 የሚያህሉ ሰዎች ጴጥሮስ የተናገረውን አምነው የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ሆኑ። እነርሱ ተጠምቀው በኢየሩሳሌም ያለችው ቤተ ክርስቲያን አባል ሆኑ።

ደቀ መዛሙርቱ ያለ ማቋረጥ የሐዋርያትን ትምህርት ሰሙ፣ አብረው ጊዜ አሳለፉ፣ አብረው በሉ፣ አንዳቸው ለሌላኛው ጸለዩ። አብረው እግዚአብሔርን አመሰገኑ፣ የነበራቸውንም ነገር ሁሉ እርስ በርስ ተካፈሉ። ሁሉም ሰው ስለ እነርሱ መልካም ያስብ ነበር። በየዕለቱ ብዙ ሰዎች አማኞች ሆኑ።

ข้อมูลที่เกี่ยวข้อง

สื่อบันทึกเสียงรูปแบบmp3, ซีดี, เทปคาสเซ็ท - องค์กรจีอาร์เอ็น มีสื่อบันทึกเสียงต่างๆ หลายพันภาษา เนื้อหาสื่อบันทึกเสียงตรงกับความจริงในพระคัมภีร์ เป็นเรื่องราวเกี่ยวกับความรอดและชีวิตคริสเตียน

ดาวน์โหลดฟรี - ที่นี่ท่านสามารถค้นหาบทความต่างๆ ของจีอาร์เอ็นในภาษาต่างๆ พร้อมทั้งภาพประกอบ และสื่ออื่นๆ ที่สามารถดาวน์โหลดได้

ห้องสมุดสื่อบันทึกเสียงข่าวประเสริฐของจีอาร์เอ็น - เจ็ดสิบกว่าปีที่นักบันทึกเสียงขององค์กรจีอาร์เอ็นได้บันทึกเสียงภาษาของชนกลุ่มน้อยต่างๆ และได้ผลิตสื่อบันทึกเสียงข่าวประเสริฐมากมาย

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons