unfoldingWord 49 - ዐዲሱ የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን

unfoldingWord 49 - ዐዲሱ የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን

Zusammenfassung: Genesis 3; Matthew 13-14; Mark 10:17-31; Luke 2; 10:25-37; 15; John 3:16; Romans 3:21-26, 5:1-11; 2 Corinthians 5:17-21; Colossians 1:13-14; 1 John 1:5-10

Skript Nummer: 1249

Sprache: Amharic

Zuschauer: General

Genre: Bible Stories & Teac

Zweck: Evangelism; Teaching

Bibelzitat: Paraphrase

Status: Approved

Skripte dienen als grundlegende Richtlinie für die Übersetzung und Aufnahme in anderen Sprachen. Sie sollten, soweit erforderlich, angepasst werden, um sie für die jeweilige Kultur und Sprache verständlich und relevant zu machen. Einige der verwendeten Begriffe und Konzepte müssen unter Umständen ausführlicher erklärt oder sogar ersetzt oder ganz entfernt werden.

Skript Text

አንድ መልአክ ማርያም ለተባለች ድንግል የእግዚአብሔርን ልጅ እንደምትወልድ ነገራት። ስለዚህ እርስዋ ገና ድንግል እያለች ወንድ ልጅ ወለደችና ኢየሱስ ብላ ሰየመችው። ስለዚህ ኢየሱስ አምላክም ሰውም ነው።

ኢየሱስ አምላክ መሆኑን የሚያረጋግጡ ብዙ ተአምራትን አደረገ። በውሃ ላይ ተራመደ፣ ማዕበልን ጸጥ አደረገ፣ ብዙ በሽተኞችን ፈወሰ፣ አጋንንትን አወጣ፣ ሙታንን አስነሣ፣ እንዲሁም አምስት እንጀራና ሁለት ትንንሽ ዓሣ ከ5,000 ለበለጡ ሰዎች እንዲበቃ አደረገ።

ደግሞም ኢየሱስ ታላቅ መምህር ነው፣ የእግዚአብሔር ልጅ ስለሆነም በሥልጣን ተናገረ። ራሳችሁን እንደምትወዱ ሌሎችን ሰዎችንም ውደዱ ብሎ አስተማረ።

ደግሞም እርሱ ሀብታችሁን ጨምሮ ማንኛውንም ነገር እንደምትወዱ እግዚአብሔርን መውደድ አለባችሁ ብሎ አስተማረ።

ኢየሱስ የእግዚአብሔር መንግሥት በዓለም ካለ ከማንኛውም ነገር ይልቅ የከበረች ነች አለ። ለማንኛውም ሰው እጅግ በጣም አስፈላጊው ነገር የእግዚአብሔር መንግሥት ወገን መሆን ነው። ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ለመግባት ከኃጢአታችሁ መዳን አለባችሁ።

ኢየሱስ አንዳንድ ሰዎች ተቀብለውት እንደሚድኑ፣ ሌሎች ግን እንደማይቀበሉት አስተማረ። አንዳንድ ሰዎች እንደ መልካም መሬት ናቸው አለ። የኢየሱስን የምሥራች ተቀብለው ይድናሉ። ሌሎች ሰዎች የእግዚአብሔር ቃል ዘር እንደማይገባበትና ምንም ፍሬ እንደማያፈራ በመንገድ ዳር እንዳለ አለትማ መሬት ናቸው። እነዚያ ሰዎች ስለ ኢየሱስ የሚናገረውን መልእክት የማይቀበሉና ወደ መንግሥቱ የማይገቡ ናቸው።

ኢየሱስ፣ እግዚአብሔር ኃጢአተኞችን በጣም እንደሚወድ አስተማረ። ይቅር ሊላቸውና ልጆቹ ሊያደርጋቸው ይፈልጋል።

ደግሞም ኢየሱስ እግዚአብሔር ኃጢአትን እንደሚጠላ ነግሮናል። አዳምና ሔዋን ኃጢአት በሠሩ ጊዜ፣ ኃጢአቱ ዝርያዎቻቸውን ሁሉ ጐዳ። ከዚህ የተነሣ በዓለም ያለ ሁሉም ሰው ኃጢአት ይሠራል ከእግዚአብሔርም ይለያያል። ስለዚህ ሁሉም ሰው የእግዚአብሔር ጠላት ሆኖአል።

ነገር ግን በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።

በኃጢአታችሁ ምክንያት በደለኞች ናችሁና መሞት ይገባችኋል። እግዚአብሔር በእናንተ ላይ መቈጣት ነበረበት፣ ነገር ግን ቊጣውን በእናንተ ላይ በማፍስስ ፈንታ በኢየሱስ ላይ አፈሰሰው። ኢየሱስ በመስቀል ላይ በሞተ ጊዜ፣ የእናንተን ቅጣት ተቀበለ።

ኢየሱስ ከቶ ኃጢአት አላደረገም፣ ነገር ግን የእናንተን ኃጢአትና በዓለም ያለውን የእያንዳንዱን ሰው ኃጢአት ለማስወገድ መቀጣትንና ፍጹም መሥዋዕት ሆኖ መሞትን መረጠ። ኢየሱስ ራሱን ስለ ሠዋ፣ እግዚአብሔር ማንኛውንም ኃጢአት፣ አስከፊ የሆነውን ኃጢአት እንኳ ይቅር ማለት ይችላል።

መልካም ሥራዎች ሊያድኑአችሁ አይችሉም። ከእግዚአብሔር ጋር ግንኙነት እንዲኖራችሁ ልታደርጉ የምትችሉት ምንም ነገር የለም። ኢየሱስ ብቻ ኃጢአታችሁን ሊያጥብ ይችላል። ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን፣ በእናንተ ፈንታ በመስቀል ላይ መሞቱን እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው ብቻ ማመን አለባችሁ።

እግዚአብሔር በኢየሱስ የሚያምነውንና ጌታው አድርጎ የሚቀበለውን ማንኛውንም ሰው ያድናል። ባለ ጠጎች ሆኑ ወይም ድሆች፣ ወንድ ወይም ሴት፣ ሽማግሌ ወይም ወጣት፣ ወይም የትም ብትኖሩ ምንም አይደለም። እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር የቅርብ ግንኙነት ሊኖረው ይችል ዘንድ ይወዳችኋል በኢየሱስ እንድታምኑም ይፈልጋል።

ኢየሱስ እንድታምኑና እንድትጠመቁ ይጋብዛችኋል። ኢየሱስ መሲሕ፣ ብቸኛው የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ታምናላችሁ? ኃጢአተኞች መሆናችሁንና እግዚአብሔር ቢቀጣችሁ የተገባ መሆኑን ታምናላችሁ? ኢየሱስ ኃጢአታችሁን ለማስወገድ በመስቀል ላይ መሞቱን ታምናላችሁ?

በኢየሱስና እርሱ ለእናንተ በሠራው ሥራ ብታምኑ፣ እናንተ ክርስቲያኖች ናችሁ! እግዚአብሔር ከሰይጣንና ከጨለማ መንግሥት አውጥቶአችሁ በእግዚአብሔር የብርሃን መንግሥት ውስጥ አድርጎአችኋል። እግዚአብሔር ነገሮችን የምታደርጉበትን አሮጌውንና ኃጢአተኛውን መንገዳችሁን አስወግዶ ዐዲስና ጻድቅ የሆነ የአደራረግ መንገድ ሰጥቶአችኋል።

እናንተ ክርስቲያኖች ናችሁ፣ ኢየሱስ በሠራው ሥራ ምክንያት እግዚአብሔር ኃጢአታችሁን ይቅር ብሎአችኋል። አሁን እግዚአብሔር በጠላቶች ፈንታ የቅርብ ወዳጆች አድርጎ ይቈጥራችኋል።

የእግዚአብሔር ወዳጆችና የጌታ ኢየሱስ አገልጋዮች ከሆናችሁ፣ ኢየሱስ ለሚያስተምራችሁ ነገር ትታዘዛላችሁ። ክርስቲያኖች ብትሆኑም እንኳ፣ አሁንም ኃጢአት ለመሥራት ትፈተናላችሁ። ነገር ግን እግዚአብሔር የታመነ ነውና ኃጢአታችሁን ብትናዘዙ ይቅር እላችኋለሁ ይላል። ኃጢአትን የምትቃወሙበትን ብርታት ይሰጣችኋል።

እግዚአብሔር እንድትጸልዩ፣ ቃሉን እንድታጠኑ፣ ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋር እንድታመልኩ፣ ያደረገላችሁንም ለሌሎች እንድትነግሩ ይጠይቃችኋል። እነዚህ ነገሮች ሁሉ ከእርሱ ጋር የጠለቀ ግንኙነት እንዲኖራችሁ ይረዱአችኋል።

Verwandte Informationen

Worte des Lebens - GRN hat Audio-Gospel-Botschaften in tausenden von Sprachen, beinhaltet bibelbasierte Botschaften über die Erettung und das christliche Leben.

Freie Downloads - Hier findet man alle GRN Botschaften, Schriften in vielen Sprachen, plus Bilder und andere verwandte Materialien, verfügbar zum Download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons