unfoldingWord 32 - ኢየሱስ ርኵስ መንፈስ የያዘውን ሰውና የታመመችውን ሴት ፈወሰ

unfoldingWord 32 - ኢየሱስ ርኵስ መንፈስ የያዘውን ሰውና የታመመችውን ሴት ፈወሰ

概要: Matthew 8:28-34; 9:20-22; Mark 5; Luke 8:26-48

文本编号: 1232

语言: Amharic

听众: General

类型/流派: Bible Stories & Teac

目的: Evangelism; Teaching

圣经摘录: Paraphrase

状态: Approved

脚本是翻译和录制成其他语言的基本指南,它们需要根据实际需要而进行调整以适合不同的文化和语言。某些使用术语和概念可能需要有更多的解释,甚至要完全更换或省略。

文本正文

አንድ ቀን ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ በጀልባ ሐይቁን አቋርጠው የጌርጌሴኖን ሰዎች ወደሚኖሩበት አካባቢ ሄዱ።

ወደ ሐይቁ ማዶ በደረሱ ጊዜ ርኵስ መንፈስ የያዘው ሰው ሮጦ ወደ ኢየሱስ መጣ።

ይህ ሰው ማንም ሊቈጣጠረው የማይችል እጅግ ብርቱ ነበረ። ሰዎች እጆቹንና እግሮቹን እንኳ በሰንሰለት አስረውት ነበር፣ ነገር ግን ሰንሰለቱን ይበጣጥስ ነበር።

ሰውዬው በአካባቢው ባሉ መቃብሮች መካከል ይኖር ነበር። ይህ ሰው ቀኑንና ሌሊቱን ሁሉ ይጮኽ ነበር። ልብስ አይለብስም ነበር፣ ሰውነቱንም በተደጋጋሚ በድንጋይ ይቧጭር ነበር።

ሰውዬው ወደ ኢየሱስ በመጣ ጊዜ፣ በፊቱ በጉልበቱ ወድቆ ሰገደለት። ኢየሱስ ርኵስ መንፈሱን፣ “ከዚህ ሰው ውጣ!” አለው።

ርኵስ መንፈሱ ያለበት ሰው ከፍ ባለ ድምፅ የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ሆይ፣ ከእኔ ምን ትፈልጋለህ? እባክህን አታሠቃየኝ!" ብሎ ከፍ ባለ ድምፅ ጮኸ። ከዚያም ኢየሱስ ርኵስ መንፈሱን፣ “ስምህ ማን ነው?” ብሎ ጠየቀው። እርሱም፣ “ብዙዎች ነንና ስሜ ሌጌዎን ነው” አለና መለሰ። (“ሌጌዎን” በሮማ ጦር ሠራዊት ብዙ ሺህ ወታደሮችን የያዘ ክፍል ነበር።)

ርኵሳን መናፍስቱ፣ “እባክህን ከዚህ አካባቢ አታርቀን!” ብለው ለመኑት። በአቅራቢያው ባለ ኮረብታ ላይ የእሪያ መንጋ ተሰማርቶ ነበር። ስለዚህ ርኵሳን መናፍስቱ ኢየሱስን፣ “እባክህን በዚህ ፈንታ ወደ እሪያዎቹ ስደደን!” ብለው ለመኑት። ኢየሱስ፣ “ሂዱ!” አላቸው።

ርኵሳን መናፍስቱ ከሰውዬው ወጡና ወደ እሪያዎቹ ገቡ። እሪያዎቹ ከአፋፉ ቊልቊል ሮጡና በሐይቁ ሰጠሙ። በመንጋው 2,000 ያህል እሪያዎች ነበሩ።

እሪያዎቹን ይጠብቁ የነበሩት ሰዎች የሆነውን ነገር ባዩ ጊዜ ወደ ከተማ ሮጡና ኢየሱስ ያደረገውን ነገር ላገኙት ሰው ሁሉ ተናገሩ። የከተማው ሰዎች መጡና ርኵሳን መናፍስት የነበሩበትን ሰው ዐዩ። ልብሱን ለብሶ እንደ ጤናማ ሰው ሆኖ በጸጥታ ተቀምጦ ነበር።

ሰዎቹ በጣም ፈርተው ነበርና ኢየሱስን እንዲሄድ ጠየቁት። ስለዚህ ኢየሱስ ጀልባ ውስጥ ገባና ለመሄድ ተዘጋጀ። ርኵን መናፍስት የነበሩበት ሰው ከኢየሱስ ጋር ለመሄድ ልመና አቀረበ።

ነገር ግን ኢየሱስ፣ “አይደለም፣ ወደ ቤትህ ሄደህ እግዚአብሔር ስላደረገልህ ነገር ሁሉና እንዴት እንደ ማረህ ለወዳጆችህና ለቤተ ሰብህ እንድትነግር እፈልጋለሁ” አለው።

ስለዚህ ሰውዬው ሄደና ኢየሱስ ስላደረገለት ነገር ለሁሉም ሰው ተናገረ። ታሪኩን የሰማ ሰው ሁሉ በአድናቆትና በአግራሞት ተሞላ።

ኢየሱስ ወደ ሐይቁ ማዶ ተመለሰ። እዚያ በደረሰ ጊዜ ብዙ ሕዝብ በዙሪያው ተሰበሰቡና አጨናነቁት። በሕዝቡ መካከል ለዐሥራ ሁለት ዓመት ደም ሲፈሳት የነበረች ሴት ነበረች። እንዲፈውሱአት ገንዘብዋን ሁሉ ለሐኪሞች ከፍላ ነበር፣ ነገር ግን ባሰባት።

ኢየሱስ ብዙ በሽተኞችን እንደ ፈወሰ ሰምታ ነበርና፣ “የኢየሱስን ልብስ ብቻ ብዳስስ ያኔ እኔም እንደምፈወስ እርግጠኛ ነኝ!” ብላ ዐሰበች። ስለዚህ ከኢየሱስ ኋላ መጣችና ልብሱን ዳሰሰች። ልብሱን እንደ ዳሰሰች ወዲያውኑ ደምዋ ቆመ!

ወዲያውኑ፣ ኢየሱስ ኃይል ከእርሱ እንደ ወጣ ዐወቀ። ስለዚህ ወደ ኋላ ዞረና፣ “ማን ነው የዳሰሰኝ?” ብሎ ጠየቀ። ደቀ መዛሙርቱ፣ “በዙሪያህ የተሰበሰቡና የሚያጋፉህ ብዙ ሰዎች አሉ። ‘ስለ ምን ማን ዳሰሰኝ’ ብለህ ትጠይቃለህ?” ብለው መለሱለት።

ሴቲቱ እየተንቀጠቀጠችና በጣም እየፈራች በኢየሱስ ፊት ተደፋች። ከዚያም ያደረገችውን፣ እንዲሁም የተፈወሰች መሆንዋን ነገረችው። ኢየሱስ፣ “እምነትሽ አድኖሻል። በሰላም ሂጂ” አላት።

相关信息

人生箴言 - GRN提供几千种语言的福音音频信息,包含圣经信息,救赎和基督徒生活。

免费下载 - 免费下载传福音及发展教会所用的录音、图片、文本和其他相关资料。内容包括福音与圣经故事,并已被翻译成上千种语言。

环球录音网音频图书馆 - Mp3,CD和磁带格式的福音材料和圣经教学材料,满足人们不同文化的需求。录音材料的形式多样,包括简单的圣经故事,福音信息,经文朗诵和歌曲。

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons