unfoldingWord 09 - እግዚአብሔር ሙሴን ጠራው

unfoldingWord 09 - እግዚአብሔር ሙሴን ጠራው

概要: Exodus 1-4

文本编号: 1209

语言: Amharic

听众: General

类型/流派: Bible Stories & Teac

目的: Evangelism; Teaching

圣经摘录: Paraphrase

状态: Approved

脚本是翻译和录制成其他语言的基本指南,它们需要根据实际需要而进行调整以适合不同的文化和语言。某些使用术语和概念可能需要有更多的解释,甚至要完全更换或省略。

文本正文

ዮሴፍ ከሞተ በኋላ ዘመዶቹ በሙሉ በግብፅ ቆዩ። እነርሱና ዘሮቻቸው ለብዙ ዓመታት እዚያ መኖራቸውን ቀጠሉ፤ ብዙ ልጆችንም አፈሩ፤ እነርሱ እስራኤላውያን ተብለው ተጠሩ።

ከመቶዎች ዓመታት በኋላ የእስራኤላውያን ቊጥር እየበዛ መጣ። ግብፃውያንም ዮሴፍንና እነርሱን ለመርዳት ያደረገውን ሁሉ ዘነጉ። እስራኤላውያን እየበዙ በመምጣታቸው ግብፃውያን ፈሯቸው። ስለዚህ በዚያን ጊዜ ግብፅን ያስተዳድር የነበረው ፈርዖን እስራኤሎችን ለግብፃውያን ባሪያዎች አደረጓቸው።

ግብፃውያን እስራኤላውያንን የግንብ ሥራ እንዲሠሩ፣ ከተማውን ሁሉ እንዲገነቡ በማድረግ በኃይል ያስገድዷቸው ነበር። ከባድ ሥራ ሕይወታቸውን አስቸጋሪ አደረገው። እግዚአብሔር ግን ባረካቸው ብዙ ልጆችም ነበሯቸው።

ፈርዖን እስራኤላውያን ብዙ ሕፃናት እንዳሏቸው አየ፤ ስለዚህ ፈርዖን ከእስራኤላውያን ወንዶች ልጆች ሲወለዱ አባይ ወንዝ ውስጥ በመወርወር እንዲገድሉ ሕዝቡን አዘዘ።

አንዲት እስራኤላዊት ሴት ወንድ ልጅ ወለደች፤ እርሷና ባለቤቷ የቻሉትን ያህል ልጁን ደበቁ።

የልጁ ወላጆች ልጁን ሊደብቁት ባልቻሉ ጊዜ ልጁን በሚንሳፈፍ ቅርጫት ውስጥ አድርገው በአባይ ወንዝ ዳር ባለው ቄጤማ ፊት ለፊት እንዳይገደል ሊያድኑት ወንዙ ላይ ለቀቁት። ታላቅ እህቱም የሚሆንበትን ለማየት በቅርብ ትከታተለው ነበር።

የፈርዖን ሴት ልጅ ቅርጫት አየችና በውስጡ ያለውን ተመለከተች። ሕፃኑን ባየች ጊዜ እንደ ልጇ አድርጋ ወሰደችው። እርሷም ልጁን የምትንከባከብ እስራኤላዊት ሴት ቀጠረች። የቀጠረቻትም ሴትዮ የገዛ ልጁ እናት መሆኗን ሳታውቅ ነበር። ልጁም ሲያድግና የናቱን ጡት መጥባት ባቆመ ጊዜ ሴትዮዋ ወደ ፈርዖን ልጅ መለሰችው ስሙንም “ሙሴ” ብለው ጠሩት።

አንድ ቀን ሙሴ ባደገ ጊዜ አንድ ግብፃዊ እስራኤላዊ የሆነን ባሪያ ሲመታው አየ ሙሴም እስራኤላዊ ወገኑን ሊያድነው ሞከረ።

ሙሴ ማንም የማያይ መስሎት ግብፃዊውን ገድሎ ቀበረው። ነገር ግን ሙሴ ያደረገውን አንድ ሰው አይቶታል።

ሙሴ ያደረገውን ፈርዖን በሰማ ጊዜ ሊገድለው ሞከረ። ሙሴ ግን ከፈርዖን ወታደሮች ነፍሱን ወደሚያድንበት ከግብፅ ወደ ምድረ በዳ ሸሸ።

ከግብፅ ሩቅ በሆነ ምድረ በዳ ሙሴ የበጐች እረኛ ሆነ። ከዚያም አገር ሚስት አግብቶ ሁለት ወንዶች ልጆች ወለደ።

አንድ ቀን ሙሴ በጐቹን እየጠበቀ ሳለ እሳት የሚነድበት ቊጥቋጦ ተመለከተ ይሁን እንጂ ቊጥቋጦው አልተቃጠለም፤ ሙሴም በደንብ ለማየት ወደ ቊጥቋጦው ጠጋ አለ። ወደሚቃጠለው ቊጥቋጦ ጠጋ ሲል የእግዚአብሔር ድምፅ “ሙሴ በቅዱስ ስፍራ ቆመሃልና ከእግርህ ጫማህን አውልቅ” አለው።

እግዚአብሔርም አለ “የሕዝቤን መከራ አይቻለሁና ወደ ፈርዖን እልክሃለሁ እስራኤልንም ከግብፅ ባርነት ነጻ ታወጣቸዋለህ። ለአብርሃም፣ ለይስሐቅና ለያዕቆብ ተስፋ የሰጠኋቸውን የከነዓንን ምድር እሰጣቸዋለሁ።”

ሕዝቡ ማንላከህ ብለው ቢጠይቁኝ ምን እላቸዋለሁ ሲል እግዚአብሔርን ጠየቀ። እግዚአብሔርምሙሴን “እኔ ያለሁና የምኖር ነኝ ስለዚህ‘ያለና የሚኖር’ ልኮኛልብለህ ንገራቸው” አለው።

ሙሴ ስለ ፈራ ወደ ፈርዖን መሄድ አልፈለገም። ምክንያቱም የንግግር ችሎታ የለኝም ብሎ በማሰቡ ነበር። ስለዚህም እግዚአብሔር የሙሴን ወንድም አሮንን አብሮት እንዲሄድና ሙሴን እንዲረዳው ላከው። እግዚአብሔር ሙሴንና አሮንን ፈርዖን ሕዝቡን አለቅም በሚል ልቡን ሊያደነድን እንደሚችል አስጠነቀቃቸው።

相关信息

人生箴言 - GRN提供几千种语言的福音音频信息,包含圣经信息,救赎和基督徒生活。

免费下载 - 免费下载传福音及发展教会所用的录音、图片、文本和其他相关资料。内容包括福音与圣经故事,并已被翻译成上千种语言。

环球录音网音频图书馆 - Mp3,CD和磁带格式的福音材料和圣经教学材料,满足人们不同文化的需求。录音材料的形式多样,包括简单的圣经故事,福音信息,经文朗诵和歌曲。

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons