unfoldingWord 37 - ኢየሱስ አልዓዛርን ከሞት አስነሣ

unfoldingWord 37 - ኢየሱስ አልዓዛርን ከሞት አስነሣ

Grandes lignes: John 11:1-46

Numéro de texte: 1237

Langue: Amharic

Audience: General

Genre: Bible Stories & Teac

Objectif: Evangelism; Teaching

Citation biblique: Paraphrase

Statut: Approved

Les scripts sont des directives de base pour la traduction et l'enregistrement dans d'autres langues. Ils doivent être adaptés si nécessaire afin de les rendre compréhensibles et pertinents pour chaque culture et langue différente. Certains termes et concepts utilisés peuvent nécessiter plus d'explications ou même être remplacés ou complètement omis.

Corps du texte

አንድ ቀን ኢየሱስ አልዓዛር በጣም ታሞአል የሚል መልእክት ደረሰው። አልዓዛርና ሁለቱ እኅቶቹ ማርያምና ማርታ የኢየሱስ የቅርብ ወዳጆች ነበሩ። ኢየሱስ ይህንን ወሬ በሰማ ጊዜ፣ “ይህ ሕመም ለእግዚአብሔር ክብር ነው እንጂ ለሞት አይደለም” አለ። ኢየሱስ ወዳጆቹን ይወዳቸው ነበር፣ ነገር ግን ለሁለት ቀናት በነበረበት ስፍራ ቆየ።

ሁለቱ ቀናት ካለፉ በኋላ፣ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን፣ “ወደ ይሁዳ እንሂድ” አላቸው። “ነገር ግን መምህር ሆይ፣”ልክ ከጥቂት ጊዜ በፊት በዚያ ያሉት ሕዝብ ሊገድሉህ ይፈልጉ ነበር!" ብለው ደቀ መዛሙርቱ መለሱለት። ኢየሱስ፣ “ወዳጃችን አልዓዛር አንቀላፍቶአል፣ ከእንቅልፉ ላስነሣው እሄዳለሁ” አላቸው።

የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት፣ “ጌታ ሆይ፣ አልዓዛር ተኝቶስ ከሆነ፣ ይድናል” ብለው መለሱለት። በዚያን ጊዜ ኢየሱስ በግልጽ ነገራቸው፣ “አልዓዛር ሞቶአል። እናንተ በእኔ ታምኑ ዘንድ እዚያ ባለመኖሬ ደስ ብሎኛል።”

ኢየሱስ አልዓዛር ወደ ተወለደበት ከተማ በደረሰ ጊዜ፣ አልዓዛር ከሞተ አራት ቀን ሆኖት ነበር። ማርታ ኢየሱስን ልትገናኘው ወጣችና እንዲህ አለች፣ “ጌታ ሆይ፣ አንተ እዚህ ብትኖር ኖሮ ወንድሜ አይሞትም ነበር። ነገር ግን እግዚአብሔር የምትለምነውን ሁሉ እንደሚሰጥህ አምናለሁ።”

ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰላት፣ “እኔ ትንሣኤና ሕይወት ነኝ። በእኔ የሚያምን ሁሉ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል። በእኔ የሚያምን ሁሉ ከቶ አይሞትም። ይህን ታምኛለሽን? ማርታ፣”አዎን፣ ጌታ ሆይ! አንተ መሲሑ፣ የእግዚአብሔር ልጅ መሆንህን አምናለሁ" ብላ መለሰችለት።

ከዚያም ማርያም መጣች። በኢየሱስ እግር ወደቀችና፣ “ጌታ ሆይ፣ አንተ በዚህ ኖረህ ብትሆን ኖሮ ወንድሜ ባልሞተም ነበር” አለች። ኢየሱስ፣ “አልዓዛርን ወዴት ነው ያኖራችሁት?” ብሎ ጠየቃቸው። “በመቃብር ነው። ናና እይ” ብለው ነገሩት። ከዚያም ኢየሱስ አለቀሰ።

መቃብሩ ዋሻ ነበር፣ ድንጋይም ተገጥሞበት ነበር። ኢየሱስ ወደ መቃብሩ በደረሰ ጊዜ ድንጋዩን አንከባሉት" ብሎ ነገራቸው። ነገር ግን ማርታ፣ “ከሞተ አራት ቀን ሆኖታል። አሁን ይሸታል” አለችው።

ኢየሱስ፣ “በእኔ ብታምኚስ የእግዚአብሔርን ክብር እንድታዪ አልነገርኩሽምን?” አላት። ስለዚህ ድንጋዩን አንከባለሉት።

ከዚያ በኋላ ኢየሱስ ወደ ላይ ተመለከተና፣ “አባት ሆይ፣ ስለምትሰማኝ አመሰግንሃለሁ። አንተ ሁልጊዜ እንደምትሰማኝ ዐውቃለሁ፣ ነገር ግን አንተ እንደ ላክኸኝ ያምኑ ዘንድ እዚህ ስለ ቆሙት ስለ እነዚህ ሰዎች ሁሉ ይህን እላለሁ” አለ። ከዚያም ኢየሱስ፣ “አልዓዛር ሆይ፣ ወደ ውጭ ና!” ብሎ ጮኸ።

ስለዚህ አልዓዛር ወጣ! በከፈን እንደ ተገነዘ ነበር። ኢየሱስም፣ “ፍቱትና ይሂድ ተዉት!” አላቸው። ከአይሁድ ብዙዎች በዚህ ተአምር ምክንያት በኢየሱስ አመኑ።

ነገር ግን የአይሁድ የሃይማኖት መሪዎች ቀኑ፣ ስለዚህ ኢየሱስንና አልዓዛርን እንዴት መግደል እንዳለባቸው ለማቀድ በአንድ ላይ ተሰበሰቡ።

Informations reliées

Mots de Vie - GRN présente des messages sonores évangéliques dans des milliers de langues à propos du salut et de la vie chrétienne.

Téléchargements gratuits - Ici vous allez trouver le texte pour les principaux messages GRN en plusieurs langues, plus des images et autres documents prêts à télécharger

La collection d'Enregistrements de GRN - Matériel d'évangélisation et d'enseignement biblique de base adapté aux besoins et à la culture du peuple, dans une variété de styles et de formats.

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?