unfoldingWord 26 - ኢየሱስ አገልግሎቱን ጀመረ
![unfoldingWord 26 - ኢየሱስ አገልግሎቱን ጀመረ](https://static.globalrecordings.net/300x200/z42_Lk_04_13.jpg)
概要: Matthew 4:12-25; Mark 1-3; Luke 4
文本編號: 1226
語言: Amharic
聽眾: General
目的: Evangelism; Teaching
Features: Bible Stories; Paraphrase Scripture
狀態: Approved
腳本是翻譯和錄製成其他語言的基本指南,它們需要根據實際需要而進行調整以適合不同的文化和語言。某些使用術語和概念可能需要有更多的解釋,甚至要完全更換或省略。
文本文字
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z42_Lk_04_09.jpg)
ኢየሱስ የሰይጣንን ፈተና ካሸፈነ በኋላ፣ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ይኖርበት ወደ ነበረው ወደገሊላ አውራጃ ተመለሰ። ኢየሱስ ከቦታ ወደ ቦታ እየሄደ አስተማረ።ሁሉም ሰው ስለ እርሱ መልካም ይናገሩ ነበር።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z42_Lk_04_10.jpg)
ኢየሱስ በልጅነቱ ወደ ኖረበት ወደ ናዝሬትከተማ ተመለሰ። በሰንበት ወደ አምልኮ ቦታ ሄደ።ያነብ ዘንድ የነቢዩን የኢሳይያስን ጥቅልልጽሑፍ ሰጡት። ኢየሱስ ጥቅልል ጽሑፉን ከፍቶ በከፊል ለሕዝቡ አነበበላቸው።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z42_Lk_04_11.jpg)
ኢየሱስ፣ “ለድሆች የምሥራችን፣ ለተማረኩት ነጻትን፣ ለዕውሮች ማየትን፣ ለታሰሩትም መፈታትን እሰብክዘንድ እግዚአብሔር መንፈሱን ሰጥቶኛል።ይህች የተወደደችውየጌታ ዓመት ነች” ብሎ አነበበ።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z42_Lk_04_13.jpg)
ከዚያም ኢየሱስ ተቀመጠ። ሁላቸውም በቅርበት ተመለከቱት። ልክ አሁን ያነበበው የእግዚአብሔር ቃል ምንባብ መሲሑን ያመለክት ነበር። ኢየሱስ፣“ይህ ያነበብኩላችሁ ቃል ልክአሁን እየተፈጸመ ነው” አለ።ሕዝቡ ሁሉ ተደነቁ። “ይህ የዮሴፍ ልጅ አይደለምን?” አሉ።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z42_Lk_04_15.jpg)
ከዚያም ኢየሱስ፣“ነቢይ በገዛ አገሩ እንደማይከበር እውነትነው፣ በነቢዩ ኤልያስ ዘመን፣ በእስራኤል ብዙ መበለቶች ነበሩ።ነገር ግን ለሦስትዓመት ተኩል ዝናብ ባልዘነበ ጊዜ እግዚአብሔር ኤልያስን በተለየአገር እንጂ በእስራኤልያለች መበለትን እንዲረዳ አልላከውም።”
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z42_Lk_04_17.jpg)
ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መናገሩን ቀጠለ፣ “በነቢዩ ኤልሳዕ ዘመንም በእስራኤል የቆዳ ሕመም የያዛቸው ብዙ ሰዎች ነበሩ። ነገር ግን ኤልሳዕ አንዳቸውንም አልፈወሰም። የእስራኤል ጠላቶች አዛዥ የነበረውን የንዕማንን ቆዳ በሽታ ብቻ ፈወሰ።” ኢየሱስን ይሰሙ የነበሩት ሕዝብ አይሁዳውያን ነበሩ። ስለዚህ ይህን ሲናገር በሰሙት ጊዜ ተናደዱበት።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z42_Lk_04_18.jpg)
የናዝሬት ሕዝብ ኢየሱስን ከአምልኮው ቦታ ጐተቱትና ወርውረው ሊገድሉት ወደ ተራራውአፋፍ ወሰዱት።ነገር ግን ኢየሱስ በሕዝቡ መካከል ተራመደና ወደ ናዝሬትከተማ ሄደ።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z42_LK_04_22.jpg)
ከዚያም ኢየሱስ በገሊላ አውራጃ ሁሉ ተዘዋወረ፣ ብዙ ሕዝብም ወደ እርሱ መጡ። ማየት፣ መራመድ፣ መስማት፣ ወይም መናገር የማይችሉትን ጨምሮ ብዙ የታመሙ ወይም የአካል ጕዳተኞች የሆኑ ሰዎችን አመጡ።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z41_Mk_09_22.jpg)
አጋንንት የነበሩባቸው ብዙ ሰዎችን ወደ ኢየሱስ አመጡ። በኢየሱስ ትእዛዝ አጋንንቱ ከሰዎቹ ወጡ፣ ብዙ ጊዜም፣ “አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ!” ብለው ጮኹ። ሕዝቡ ተደነቁና እግዚአብሔርን አመለኩ።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_10_01.jpg)
ከዚያም ኢየሱስደቀ መዛሙርቱ ተብለው የተጠሩትን ዐሥራ ሁለት ሰዎች መረጠ። ሐዋርያቱ ከኢየሱስ ጋር ተጓዙና ከእርሱ ተማሩ።