Izberite jezik

mic

unfoldingWord 33 - የአርሶ አደሩ ታሪክ

unfoldingWord 33 - የአርሶ አደሩ ታሪክ

Oris: Matthew 13:1-23; Mark 4:1-20; Luke 8:4-15  

Številka scenarija: 1233

Jezik: Amharic

Občinstvo: General

Namen: Evangelism; Teaching

Features: Bible Stories; Paraphrase Scripture

Stanje: Approved

Skripte so osnovne smernice za prevajanje in snemanje v druge jezike. Po potrebi jih je treba prilagoditi, da bodo razumljive in ustrezne za vsako različno kulturo in jezik. Nekatere uporabljene izraze in koncepte bo morda treba dodatno razložiti ali pa jih bo treba celo zamenjati ali popolnoma izpustiti.

Besedilo scenarija

አንድ ቀን ኢየሱስ በሐይቁ ዳርቻ አጠገብ በጣም ብዙ ሕዝብ እያስተማረ ነበር። ኢየሱስ ሊናገራቸው በቂ ቦታ ለማግኘት በውሃው ዳርቻ በጀልባ ገብቶ እስኪቀመጥ ድረስ በጣም ብዙ ሰዎች ሊሰሙት መጡ። በጀልባው ተቀመጠና ሕዝቡን አስተማረ።

ኢየሱስ ይህንን ታሪክ ተናገረ። “አንድ አርሶ አደር ዘር ሊዘራ ወጣ። በእጁ ዘሩን ሲዘራ አንዳንዱ በመንገድ ዳር ወደቀ፣ ወፎችም መጥተው ያን ዘር በሙሉ በሉት።”

“ሌላው ዘር ብዙ መሬት በሌለበት በአለታማ መሬት ላይ ወደቀ፣ ነገር ግን ሥሩ ወደ መሬት መጥለቅ አልቻለም። ፀሐይዋ በወጣችና በሞቀች ጊዜ፣ ቡቃያው ጠወለገና ደረቀ።”

“አሁንም ሌላው ዘር በእሾኽ መካከል ወደቀ። ይህ ዘር መብቀል ጀመረ፣ ነገር ግን እሾኹ አነቀው። ስለዚህ በእሾኻማው መሬት ላይ የበቀለው ቡቃያ ምንም ፍሬ አላፈራም።”

“ሌላው ዘር በመልካም መሬት ላይ ወደቀ። ይህ ዘር በቀለና አንዱ 30፣ አንዱ 60፣ አንዱም መቶ ፍሬ ሰጠ። ጆሮ ያለው ይስማ!”

ይህ ታሪክ ደቀ መዛሙርቱን ግራ አጋባቸው። ስለዚህ ኢየሱስ እንዲህ ብሎ አብራራላቸው፣ “ዘሩ የእግዚአብሔር ቃል ነው። የመንገዱ ዳር የእግዚአብሔርን ቃል የሚሰማ ሰው ነው፣ ነገር ግን አያስተውለውም፣ ዲያብሎስም ቃሉን ይወስድበታል።”

“በአለታማ መሬት የተዘራው ዘር የእግዚአብሔርን ቃል ሰምቶ በደስታ የሚቀበለው ሰው ነው። ነገር ግን መከራ ወይም ስደት በሚያጋጥመው ጊዜ እምነቱን ይተዋል።”

“እሾኻማው መሬት የእግዚአብሔርን ቃል የሚሰማ ሰው ነው፣ ነገር ግን ከጊዜ በኋላ የዚህ ዓለም ዐሳብ፣ ባለጠግነትና ደስታ ለእግዚአብሔር ያለውን ፍቅር ያንቃል። ከዚህ የተነሣ፣ የሰማው ትምህርት ፍሬ አያፈራም።

“መልካሙ መሬት ግን የእግዚአብሔርን ቃል የሚሰማ፣ የሚያምነውና ፍሬ የሚያፈራ ሰው ነው።”

Povezane informacije

Besede življenja - Zvočna evangelijska sporočila v tisočih jezikih, ki vsebujejo biblijska sporočila o odrešenju in krščanskem življenju.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares its audio, video and written scripts under Creative Commons