unfoldingWord 33 - የአርሶ አደሩ ታሪክ

unfoldingWord 33 - የአርሶ አደሩ ታሪክ

Omrids: Matthew 13:1-23; Mark 4:1-20; Luke 8:4-15  

Script nummer: 1233

Sprog: Amharic

Publikum: General

Genre: Bible Stories & Teac

Formål: Evangelism; Teaching

Bibel citat: Paraphrase

Status: Approved

Scripts er grundlæggende retningslinjer for oversættelse og optagelse til andre sprog. De bør tilpasses efter behov for at gøre dem forståelige og relevante for hver kultur og sprog. Nogle anvendte termer og begreber kan have behov for mere forklaring eller endda blive erstattet eller helt udeladt.

Script tekst

አንድ ቀን ኢየሱስ በሐይቁ ዳርቻ አጠገብ በጣም ብዙ ሕዝብ እያስተማረ ነበር። ኢየሱስ ሊናገራቸው በቂ ቦታ ለማግኘት በውሃው ዳርቻ በጀልባ ገብቶ እስኪቀመጥ ድረስ በጣም ብዙ ሰዎች ሊሰሙት መጡ። በጀልባው ተቀመጠና ሕዝቡን አስተማረ።

ኢየሱስ ይህንን ታሪክ ተናገረ። “አንድ አርሶ አደር ዘር ሊዘራ ወጣ። በእጁ ዘሩን ሲዘራ አንዳንዱ በመንገድ ዳር ወደቀ፣ ወፎችም መጥተው ያን ዘር በሙሉ በሉት።”

“ሌላው ዘር ብዙ መሬት በሌለበት በአለታማ መሬት ላይ ወደቀ፣ ነገር ግን ሥሩ ወደ መሬት መጥለቅ አልቻለም። ፀሐይዋ በወጣችና በሞቀች ጊዜ፣ ቡቃያው ጠወለገና ደረቀ።”

“አሁንም ሌላው ዘር በእሾኽ መካከል ወደቀ። ይህ ዘር መብቀል ጀመረ፣ ነገር ግን እሾኹ አነቀው። ስለዚህ በእሾኻማው መሬት ላይ የበቀለው ቡቃያ ምንም ፍሬ አላፈራም።”

“ሌላው ዘር በመልካም መሬት ላይ ወደቀ። ይህ ዘር በቀለና አንዱ 30፣ አንዱ 60፣ አንዱም መቶ ፍሬ ሰጠ። ጆሮ ያለው ይስማ!”

ይህ ታሪክ ደቀ መዛሙርቱን ግራ አጋባቸው። ስለዚህ ኢየሱስ እንዲህ ብሎ አብራራላቸው፣ “ዘሩ የእግዚአብሔር ቃል ነው። የመንገዱ ዳር የእግዚአብሔርን ቃል የሚሰማ ሰው ነው፣ ነገር ግን አያስተውለውም፣ ዲያብሎስም ቃሉን ይወስድበታል።”

“በአለታማ መሬት የተዘራው ዘር የእግዚአብሔርን ቃል ሰምቶ በደስታ የሚቀበለው ሰው ነው። ነገር ግን መከራ ወይም ስደት በሚያጋጥመው ጊዜ እምነቱን ይተዋል።”

“እሾኻማው መሬት የእግዚአብሔርን ቃል የሚሰማ ሰው ነው፣ ነገር ግን ከጊዜ በኋላ የዚህ ዓለም ዐሳብ፣ ባለጠግነትና ደስታ ለእግዚአብሔር ያለውን ፍቅር ያንቃል። ከዚህ የተነሣ፣ የሰማው ትምህርት ፍሬ አያፈራም።

“መልካሙ መሬት ግን የእግዚአብሔርን ቃል የሚሰማ፣ የሚያምነውና ፍሬ የሚያፈራ ሰው ነው።”

Relateret information

Free downloads - Here you can find all the main GRN message scripts in several languages, plus pictures and other related materials, available for download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons