unfoldingWord 28 - ባለ ጠጋው ወጣት
Oris: Matthew 19:16-30; Mark 10:17-31; Luke 18:18-30
Številka scenarija: 1228
Jezik: Amharic
Občinstvo: General
Žanr: Bible Stories & Teac
Namen: Evangelism; Teaching
Svetopisemski citat: Paraphrase
Stanje: Approved
Skripte so osnovne smernice za prevajanje in snemanje v druge jezike. Po potrebi jih je treba prilagoditi, da bodo razumljive in ustrezne za vsako različno kulturo in jezik. Nekatere uporabljene izraze in koncepte bo morda treba dodatno razložiti ali pa jih bo treba celo zamenjati ali popolnoma izpustiti.
Besedilo scenarija
አንድ ቀንአንድ ባለጠጋወጣት ወደ ኢየሱስ መጣና፣ “ቸር መምህር፣ የዘላለምን ሕይወት እንድወርስ ምን ላድርግ?” ብሎ ጠየቀው። ኢየሱስ፣ “ስለ ምን ‘ቸር’ ትለኛለህ? ቸርአንድ ብቻአለ፣ እርሱም እግዚአብሔር ነው።ነገር ግንአንተ የዘላለም ሕይወት እንዲኖርህ ከፈለግህ ለእግዚአብሔር ሕግታዘዝ” አለው።
“የትኞቹን ልታዘዝ?” ብሎ ጠየቀው። ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰለት፣ “አትግደል። አታመንዝር። አትስረቅ። አትዋሽ። አባትህንና እናትህን አክብር፣ ባልጀራህንምእንደ ራስህ ውደድ።”
ነገር ግን ወጣቱ፣ “ከልጅነቴጀምሮ እነዚህንሕጎች ሁሉ ፈጽሜአለሁ። ለዘላለም ለመኖርሌላስ ምን ማድረግ ያስፈልገኛል?” አለ። ኢየሱስ ዐየውና ወደደው።
ኢየሱስ፣ “ፍጹም ለመሆን ብትፈልግ፣ ያለህን ንብረት ሁሉሽጥና ገንዘቡን ለድሆች ስጥ፣ በሰማይም መዝገብ ታገኛለህ። ከዚያም በኋላ ናና ተከተለኝ” ብሎመለሰለት።
ወጣቱ፣ ኢየሱስ የተናገረውን በሰማ ጊዜ፣ በጣም ባለ ጠጋ ነበርና ያለውን ነገር ሁሉ መስጠት ስላልፈለገ በጣም ዐዘነ። ከኢየሱስ ፊቱን አዞረና ሄደ።
በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን እንዲህ አላቸው፣ “ለባለ ጠጎች ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት እጅግ አስቸጋሪ ነው! አዎ፣ ባለ ጠጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ይልቅ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢያልፍ ይቀላል።”
ደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስ የተናገረውን በሰሙ ጊዜ ደነገጡና፣ “ታዲያ ማን ሊድን ይችላል?” አሉ።
ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ተመለከተና፣ “ይህ በሰው ዘንድ አይቻልም፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ሁሉ ይቻላል” አለ።
ጴጥሮስ ኢየሱስን፣ “እኛ ሁሉን ትተን ተከተልንህ። ዋጋችን ምን ይሆን?” አለው።
ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰለት፣ “ስለ እኔ ቤቶችን፣ ወንድሞችን፣ እኅቶችን፣ አባትን፣ እናትን ወይም ንብረትን የተወ ሁሉ መቶ እጥፍ ይቀበላል የዘላለምንም ሕይወት ይወርሳል። ነገር ግን ፊተኞች የሆኑ ብዙዎች ኋለኞች፣ ኋለኞችም የሆኑ ብዙዎች ፊተኞች ይሆናሉ።”