unfoldingWord 28 - ባለ ጠጋው ወጣት

Contur: Matthew 19:16-30; Mark 10:17-31; Luke 18:18-30
Numărul scriptului: 1228
Limba: Amharic
Public: General
Scop: Evangelism; Teaching
Features: Bible Stories; Paraphrase Scripture
Stare: Approved
Scripturile sunt linii directoare de bază pentru traducerea și înregistrarea în alte limbi. Acestea ar trebui adaptate după cum este necesar pentru a le face ușor de înțeles și relevante pentru fiecare cultură și limbă diferită. Unii termeni și concepte utilizate pot necesita mai multe explicații sau chiar pot fi înlocuite sau omise complet.
Textul scenariului

አንድ ቀንአንድ ባለጠጋወጣት ወደ ኢየሱስ መጣና፣ “ቸር መምህር፣ የዘላለምን ሕይወት እንድወርስ ምን ላድርግ?” ብሎ ጠየቀው። ኢየሱስ፣ “ስለ ምን ‘ቸር’ ትለኛለህ? ቸርአንድ ብቻአለ፣ እርሱም እግዚአብሔር ነው።ነገር ግንአንተ የዘላለም ሕይወት እንዲኖርህ ከፈለግህ ለእግዚአብሔር ሕግታዘዝ” አለው።

“የትኞቹን ልታዘዝ?” ብሎ ጠየቀው። ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰለት፣ “አትግደል። አታመንዝር። አትስረቅ። አትዋሽ። አባትህንና እናትህን አክብር፣ ባልጀራህንምእንደ ራስህ ውደድ።”

ነገር ግን ወጣቱ፣ “ከልጅነቴጀምሮ እነዚህንሕጎች ሁሉ ፈጽሜአለሁ። ለዘላለም ለመኖርሌላስ ምን ማድረግ ያስፈልገኛል?” አለ። ኢየሱስ ዐየውና ወደደው።

ኢየሱስ፣ “ፍጹም ለመሆን ብትፈልግ፣ ያለህን ንብረት ሁሉሽጥና ገንዘቡን ለድሆች ስጥ፣ በሰማይም መዝገብ ታገኛለህ። ከዚያም በኋላ ናና ተከተለኝ” ብሎመለሰለት።

ወጣቱ፣ ኢየሱስ የተናገረውን በሰማ ጊዜ፣ በጣም ባለ ጠጋ ነበርና ያለውን ነገር ሁሉ መስጠት ስላልፈለገ በጣም ዐዘነ። ከኢየሱስ ፊቱን አዞረና ሄደ።

በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን እንዲህ አላቸው፣ “ለባለ ጠጎች ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት እጅግ አስቸጋሪ ነው! አዎ፣ ባለ ጠጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ይልቅ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢያልፍ ይቀላል።”

ደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስ የተናገረውን በሰሙ ጊዜ ደነገጡና፣ “ታዲያ ማን ሊድን ይችላል?” አሉ።

ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ተመለከተና፣ “ይህ በሰው ዘንድ አይቻልም፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ሁሉ ይቻላል” አለ።

ጴጥሮስ ኢየሱስን፣ “እኛ ሁሉን ትተን ተከተልንህ። ዋጋችን ምን ይሆን?” አለው።

ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰለት፣ “ስለ እኔ ቤቶችን፣ ወንድሞችን፣ እኅቶችን፣ አባትን፣ እናትን ወይም ንብረትን የተወ ሁሉ መቶ እጥፍ ይቀበላል የዘላለምንም ሕይወት ይወርሳል። ነገር ግን ፊተኞች የሆኑ ብዙዎች ኋለኞች፣ ኋለኞችም የሆኑ ብዙዎች ፊተኞች ይሆናሉ።”