unfoldingWord 40 - ኢየሱስ ተሰቀለ
ዝርዝር: Matthew 27:27-61; Mark 15:16-47; Luke 23:26-56; John 19:17-42
የስክሪፕት ቁጥር: 1240
ቋንቋ: Amharic
ታዳሚዎች: General
ዓላማ: Evangelism; Teaching
Features: Bible Stories; Paraphrase Scripture
ሁኔታ: Approved
ስክሪፕቶች ወደ ሌሎች ቋንቋዎች ለመተርጎም እና ለመቅዳት መሰረታዊ መመሪያዎች ናቸው። ለእያንዳንዱ የተለየ ባህል እና ቋንቋ እንዲረዱ እና እንዲስማሙ ለማድረግ እንደ አስፈላጊነቱ ማስተካከል አለባቸው። አንዳንድ ጥቅም ላይ የዋሉ ቃላቶች እና ጽንሰ-ሐሳቦች የበለጠ ማብራሪያ ሊፈልጉ ወይም ሊተኩ ወይም ሙሉ ለሙሉ ሊተዉ ይችላሉ.
የስክሪፕት ጽሑፍ
ወታደሮቹ በኢየሱስ ላይ ከዘበቱ በኋላ፣ ሊሰቅሉት ወሰዱት። የሚሞትበትን እንዲሸከም አደረጉት።
ወታደሮቹ ኢየሱስን “የራስ ቅል” ተብሎ ወደሚጠራ ስፍራ አመጡትና እጆቹንና እግሮቹን በመስቀል ላይ ጠረቁአቸው። ኢየሱስ ግን፣ “አባት ሆይ፣ የሚያደርጉትን ዐያውቁምና ይቅር በላቸው” አለ። ጲላጦስ፣ በምልክት ላይ፣ “የአይሁድ ንጉሥ” ብለው እንዲጽፉና ከኢየሱስ ራስ በላይ በመስቀሉ ላይ እንዲያኖሩት አዘዘ።
ወታደሮቹ በኢየሱስ ልብስ ላይ ዕጣ ተጣጣሉ። ይህንን ባደረጉበት ጊዜ፣ “ልብሶቼን ተከፋፈሉ፣ በልብሴም ላይ ዕጣ ተጣጣሉ” የሚለውን ትንቢት ፈጸሙ።
ኢየሱስ በሁለት ወንበዴዎች መካከል ተሰቀለ። አንደኛው በኢየሱስ ላይ ዘበተበት፣ ሌላኛው ግን፣ “አንተ እግዚአብሔርን አትፈራም? እኛ በደለኞች ነን፣ ይህ ሰው ግን በደል የለበትም” አለ። ከዚያም ኢየሰስን፣ “እባክህን በመንግሥትህ ዐስበኝ” አለው። ኢየሱስ፣ “ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትሆናለህ” ብሎ መለሰለት።
የአይሁድ መሪዎችና በሕዝቡ መካከል የነበሩ ሌሎች ሰዎች በኢየሱስ ላይ ተዘባበቱበት። “የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ ከመስቀል ላይ ውረድና ራስህን አድን! ከዚያ በኋላ እናምንብሃለን” አሉት።
በዚያን ጊዜ እኩለ ቀን ቢሆንም፣ በአካባቢው ሁሉ ላይ ሰማዩ ፍጹም ጨለማ ሆነ። ከእኩለ ቀን እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ እንደ ጨለመ ቆየ።
ከዚያ በኋላ ኢየሱስ፣ “ተፈጸመ! አባት ሆይ፣ ነፍሴን በእጅህ እሰጣለሁ” ብሎ ጮኸ። ከዚያም ራሱን አዘነበለና መንፈሱን ሰጠ። በሞተ ጊዜ የምድር መንቀጥቀጥ ሆነ፣ በቤተ መቅደስ የነበረው ሕዝቡን ከእግዚአብሔር መገኘት የለየው ትልቁ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ለሁለት ተቀደደ።
ኢየሱስ በሞቱ በኩል ወደ እግዚአብሔር እንዲመጡ ለሰዎች መንገድ ከፈተላቸው። ኢየሱስን ይጠብቅ የነበረው ወታደር የሆነውን ሁሉ ባየ ጊዜ፣ “በእርግጥ ይህ ሰው በደል የለበትም። የእግዚአብሔር ልጅ ነው” አለ።
በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መሲሕ መሆኑን ያመኑ ሁለት የአይሁድ መሪዎች፣ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ የኢየሱስን ሥጋ እንዲሰጣቸው ጲላጦስን ለመኑት። ሥጋውን በጨርቅ ገነዙትና ከአለት በተወቀረ መቃብር አኖሩት። ከዚያም ክፍቱን ስፍራ ለመዝጋት ከመቃብሩ ፊት ለፊት ትልቅ ድንጋይ አንከባለሉ።