unfoldingWord 40 - ኢየሱስ ተሰቀለ

unfoldingWord 40 - ኢየሱስ ተሰቀለ

Zusammenfassung: Matthew 27:27-61; Mark 15:16-47; Luke 23:26-56; John 19:17-42

Skript Nummer: 1240

Sprache: Amharic

Zuschauer: General

Genre: Bible Stories & Teac

Zweck: Evangelism; Teaching

Bibelzitat: Paraphrase

Status: Approved

Skripte dienen als grundlegende Richtlinie für die Übersetzung und Aufnahme in anderen Sprachen. Sie sollten, soweit erforderlich, angepasst werden, um sie für die jeweilige Kultur und Sprache verständlich und relevant zu machen. Einige der verwendeten Begriffe und Konzepte müssen unter Umständen ausführlicher erklärt oder sogar ersetzt oder ganz entfernt werden.

Skript Text

ወታደሮቹ በኢየሱስ ላይ ከዘበቱ በኋላ፣ ሊሰቅሉት ወሰዱት። የሚሞትበትን እንዲሸከም አደረጉት።

ወታደሮቹ ኢየሱስን “የራስ ቅል” ተብሎ ወደሚጠራ ስፍራ አመጡትና እጆቹንና እግሮቹን በመስቀል ላይ ጠረቁአቸው። ኢየሱስ ግን፣ “አባት ሆይ፣ የሚያደርጉትን ዐያውቁምና ይቅር በላቸው” አለ። ጲላጦስ፣ በምልክት ላይ፣ “የአይሁድ ንጉሥ” ብለው እንዲጽፉና ከኢየሱስ ራስ በላይ በመስቀሉ ላይ እንዲያኖሩት አዘዘ።

ወታደሮቹ በኢየሱስ ልብስ ላይ ዕጣ ተጣጣሉ። ይህንን ባደረጉበት ጊዜ፣ “ልብሶቼን ተከፋፈሉ፣ በልብሴም ላይ ዕጣ ተጣጣሉ” የሚለውን ትንቢት ፈጸሙ።

ኢየሱስ በሁለት ወንበዴዎች መካከል ተሰቀለ። አንደኛው በኢየሱስ ላይ ዘበተበት፣ ሌላኛው ግን፣ “አንተ እግዚአብሔርን አትፈራም? እኛ በደለኞች ነን፣ ይህ ሰው ግን በደል የለበትም” አለ። ከዚያም ኢየሰስን፣ “እባክህን በመንግሥትህ ዐስበኝ” አለው። ኢየሱስ፣ “ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትሆናለህ” ብሎ መለሰለት።

የአይሁድ መሪዎችና በሕዝቡ መካከል የነበሩ ሌሎች ሰዎች በኢየሱስ ላይ ተዘባበቱበት። “የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ ከመስቀል ላይ ውረድና ራስህን አድን! ከዚያ በኋላ እናምንብሃለን” አሉት።

በዚያን ጊዜ እኩለ ቀን ቢሆንም፣ በአካባቢው ሁሉ ላይ ሰማዩ ፍጹም ጨለማ ሆነ። ከእኩለ ቀን እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ እንደ ጨለመ ቆየ።

ከዚያ በኋላ ኢየሱስ፣ “ተፈጸመ! አባት ሆይ፣ ነፍሴን በእጅህ እሰጣለሁ” ብሎ ጮኸ። ከዚያም ራሱን አዘነበለና መንፈሱን ሰጠ። በሞተ ጊዜ የምድር መንቀጥቀጥ ሆነ፣ በቤተ መቅደስ የነበረው ሕዝቡን ከእግዚአብሔር መገኘት የለየው ትልቁ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ለሁለት ተቀደደ።

ኢየሱስ በሞቱ በኩል ወደ እግዚአብሔር እንዲመጡ ለሰዎች መንገድ ከፈተላቸው። ኢየሱስን ይጠብቅ የነበረው ወታደር የሆነውን ሁሉ ባየ ጊዜ፣ “በእርግጥ ይህ ሰው በደል የለበትም። የእግዚአብሔር ልጅ ነው” አለ።

በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መሲሕ መሆኑን ያመኑ ሁለት የአይሁድ መሪዎች፣ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ የኢየሱስን ሥጋ እንዲሰጣቸው ጲላጦስን ለመኑት። ሥጋውን በጨርቅ ገነዙትና ከአለት በተወቀረ መቃብር አኖሩት። ከዚያም ክፍቱን ስፍራ ለመዝጋት ከመቃብሩ ፊት ለፊት ትልቅ ድንጋይ አንከባለሉ።

Verwandte Informationen

Worte des Lebens - GRN hat Audio-Gospel-Botschaften in tausenden von Sprachen, beinhaltet bibelbasierte Botschaften über die Erettung und das christliche Leben.

Freie Downloads - Hier findet man alle GRN Botschaften, Schriften in vielen Sprachen, plus Bilder und andere verwandte Materialien, verfügbar zum Download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons