unfoldingWord 42 - ኢየሱስ ወደ ሰማይ ተመለሰ

unfoldingWord 42 - ኢየሱስ ወደ ሰማይ ተመለሰ

طرح کلی: Matthew 28:16-20; Mark 16:12-20; Luke 24:13-53; John 20:19-23; Acts 1:1-11

شماره کتاب: 1242

زبان: Amharic

مخاطبان: General

نوع: Bible Stories & Teac

هدف: Evangelism; Teaching

نقل قول کتاب مقدس: Paraphrase

وضعیت: Approved

اسکریپت ها( سندها)، دستورالعمل های اساسی برای ترجمه و ضبط به زبان های دیگر هستند. آنها باید در صورت لزوم تطبیق داده شوند تا برای هر فرهنگ و زبان مختلف قابل درک و مرتبط باشند. برخی از اصطلاحات و مفاهیم مورد استفاده ممکن است نیاز به توضیح بیشتری داشته باشند، یا جایگزین، یا به طور کامل حذف شوند.

متن کتاب

ኢየሱስ ከሙታን በተነሣበት ቀን ከደቀ መዛሙርቱ ሁለቱ በአቅራቢያው ወዳለች ከተማ እየሄዱ ነበር። ሲጓዙም፣ በኢየሱስ ላይ ስለ ደረሰው ነገር ተነጋገሩ። እርሱ መሲሕ እንደ ሆነ ተስፋ አድርገው ነበር፣ ነገር ግን ያኔ እርሱ ተገደለ። አሁን ሴቶቹ እንደ ገና ሕያው ሆኖአል አሉ። ሁለቱ ደቀ መዛሙርት የሚያምኑትን ነገር ዐላወቁም።

ኢየሱስ ወደ እነርሱ ቀረበና አብሮአቸው ይጓዝ ጀመር፣ እነርሱ ግን ዐላወቁትም። ስለ ምን ይነጋገሩ እንደ ነበረ ጠየቃቸው፣ እነርሱም ባለፉት ጥቂት ቀናት ኢየሱስን በሚመለከት ስለ ሆኑት አስደናቂ ነገሮች ሁሉ ነገሩት። በኢየሩሳሌም የሆነውን ነገር ከማያውቅ እንግዳ ጋር ይነጋገሩ እንደ ነበር ዐሰቡ።

ከዚያም ኢየሱስ፣ ስለ መሲሑ የእግዚአብሔር ቃል የተናገረውን አብራራላቸው። መሲሑ መከራ እንደሚቀበልና እንደሚገደል፣ ነገር ግን በሦስተኛው ቀን እንደሚነሣ ነቢያት የተናገሩትን አስታወሳቸው። ሁለቱ ሰዎች ሊያድሩባት ወዳሰቡአት ከተማ ሲደርሱ፣ ጊዜው ሊመሽ ምንም ያህል አልቀረውም ነበር።

ሁለቱ ሰዎች ከእነርሱ ጋር እንዲያድር ጋበዙት፣ እርሱም ግብዣቸውን ተቀበለ። እራት ለመብላት በተዘጋጁ ጊዜ ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ እግዚአብሔርን አመሰገነ፣ ከዚያም ቈረሰው። በድንገትም ኢየሱስ መሆኑን ዐወቁ። ነገር ግን በዚያን ጊዜ እርሱ ከዓይናቸው ተሰወረ።

ሁለቱ ሰዎች፣ “ኢየሱስ ነው! የእግዚአብሔርን ቃል ሲያብራራልን ልባችን ሲቃጠልብን የነበረው ስለዚህ ነው!” ተባባሉ። ወዲያውኑ፣ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ። በደረሱ ጊዜም ለደቀ መዛሙርቱ፣ “ኢየሱስ ሕያው ነው! ዐይተነዋል!” ብለው ነገሩአቸው።

ደቀ መዛሙርቱ እየተነጋገሩ እያሉ፣ ኢየሱስ በድንገት በነበሩበት ክፍል በመካከላቸው ታየና፣ “ሰላም ለእናንተ ይሁን!” አላቸው። ደቀ መዛሙርቱ መንፈስ መሰላቸው፣ ኢየሱስ ግን፣ “ለምን ትፈራላችሁ ትጠራጠራላችሁም? እጆቼንና እግሮቼን እዩ። መናፍስት እንደ እኔ አካል የላቸውም” አላቸው። መንፈስ አለመሆኑን ለማረጋገጥ የሚበላ ነገር እንዲሰጡት ጠየቃቸው። እነርሱም ከተጠበሰ ዓሣ አንድ ቊራጭ ሰጡት፣ በላም።

ኢየሱስም፣ “በእግዚአብሔር ቃል ስለ እኔ የተጻፈው ሁሉ መፈጸም አለበት ብዬ ነግሬአችኋለሁ” አለ። በዚያን ጊዜ የእግዚአብሔርን ቃል እንዲረዱ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው። “መሲሑ መከራ እንደሚቀበል፣ እንደሚሞት፣ በሦስተኛው ቀን ከሙታን እንደሚነሣ ከረጅም ዘመን በፊት ተጽፎአል” አላቸው።

“ደግሞም በመጻሕፍት የኃጢአታቸውን ይቅርታ ለማግኘት ሰዎች ሁሉ ንስሐ ይገቡ ዘንድ ደቀ መዛሙርቴ እንደሚያውጁ ተጽፎአል። እነርሱ ከኢየሩሳሌም ጀምሮ ይህን ያደርጋሉ፣ ከዚያም በሁሉም ስፍራ ወዳሉ የሕዝብ ወገኖች ሁሉ ይሄዳሉ። እናንተ የእነዚህ ነገሮች ምስክሮች ናችሁ።

በቀጣዮቹ አርባ ቀናት ኢየሱስ ብዙ ጊዜ ለደቀ መዛሙርቱ ታያቸው። አንዴ ከ500 ለሚበልጡ ሰዎች በአንድ ጊዜ ታይቶአል! ሕያው መሆኑን በብዙ መንገድ ለደቀ መዛሙርቱ አረጋገጠላቸው፣ ስለ እግዚአብሔር መንግሥትም አስተማራቸው።

ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አላቸው፣ “ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጥቶኛል። ስለዚህ ሂዱ፣ የሕዝብ ወገኖችን ሁሉ በአብ፣ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፣ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲፈጽሙ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርቴ አድርጓቸው። እኔ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር እንደምሆን አስታውሱ።”

ኢየሱስ ከሙታን ከተነሣ ከአርባ ቀናት በኋላ ደቀ መዛሙርቱን፣ “መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በመጣ ጊዜ አባቴ ኃይልን እስኪሰጣችሁ ድረስ በኢየሩሳሌም ቆዩ” አላቸው። ከዚያ በኋላ ኢየሱስ ወደ ሰማይ ወጣ፣ ደመናም ከዓይናቸው ሰወረችው። ኢየሱስ በፍጥረት ሁሉ ላይ ሊገዛ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ።

اطلاعات مربوطه

کلام زندگی - جی آر اِن پیام‌های صوتی انجیل شامل پیام‌هایی بر طبق کتاب مقدس درباره رستگاری و زندگی بصورت یک مسیحی را به هزارن زبان ارائه می‌دهد.

دریافت رایگان - در این قسمت شما می‌توانید تمام پیام‌های اصلی جی آر اِن به چندین زبان، به علاوه تصاویر و دیگر مطالب مرتبط که برای دریافت موجود است را مشاهده کنید.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?