unfoldingWord 30 - ኢየሱስ አምስት ሺህ ሰዎችን መገበ

unfoldingWord 30 - ኢየሱስ አምስት ሺህ ሰዎችን መገበ

طرح کلی: Matthew 14:13-21; Mark 6:31-44; Luke 9:10-17; John 6:5-15

شماره کتاب: 1230

زبان: Amharic

مخاطبان: General

نوع: Bible Stories & Teac

هدف: Evangelism; Teaching

نقل قول کتاب مقدس: Paraphrase

وضعیت: Approved

اسکریپت ها( سندها)، دستورالعمل های اساسی برای ترجمه و ضبط به زبان های دیگر هستند. آنها باید در صورت لزوم تطبیق داده شوند تا برای هر فرهنگ و زبان مختلف قابل درک و مرتبط باشند. برخی از اصطلاحات و مفاهیم مورد استفاده ممکن است نیاز به توضیح بیشتری داشته باشند، یا جایگزین، یا به طور کامل حذف شوند.

متن کتاب

ኢየሱስ በተለያዩ ብዙ መንደሮች እንዲሰብኩና ሰዎችን እንዲያስተምሩ ሐዋርያቱን ላከ። እነርሱ ኢየሱስ ወደ ነበረበት በተመለሱጊዜ፣ ያደረጉትንነገር ነገሩት።ከዚያ በኋላ ኢየሱስ ሐይቁን ተሻግረውጸጥታ ወዳለበት ቦታ አብረውት እንዲሄዱናጥቂት እንዲያርፉ ጋበዛቸው። ስለዚህጀልባ ውስጥ ገቡና ሐይቁን ተሻገሩ።

ነገር ግን በጀልባውሲሄዱ ኢየሱስንና ደቀ መዛሙርቱን ያዩአቸው ብዙሰዎች ነበሩ። እነዚህሰዎች ሊቀድሙአቸው በባሕሩዳርቻ ሮጡ። ስለዚህ ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ ወደ ማዶ በደረሱጊዜ፣ በጣም ብዙሰዎች አስቀድመውበዚያ ተገኝተው ይጠባበቁአቸው ነበር።

ሕዝቡ ሴቶችና ልጆች ሳይቈጠሩ ከ5000 በላይ ወንዶች ነበሩ። ኢየሱስ ለሕዝቡ እጅግ አዘነላቸው። ለኢየሱስ እነዚህ ሕዝብ እረኛ እንደሌላቸው በጎች ነበሩ። ስለዚህ አስተማራቸውና በመካከላቸው የነበሩትን በሽተኞች ፈወሳቸው።

በዚያ ምሽት ደቀ መዛሙርቱ እንዲህ ብለው ነገሩት፣ “ጊዜው መሽቶአልና በአቅራቢያው ከተሞች የሉም። የሚበሉትን ነገር ይገዙ ዘንድ ሕዝቡን አሰናብታቸው።”

ኢየሱስ ግን ደቀ መዛሙርቱን፣ “የሚበሉትን እናንተ ስጡአቸው!” አላቸው። እነርሱም፣“ይህን ማድረግ እንዴት እንችላለን? ያለን አምስት እንጀራናሁለት ዓሣ ብቻ ነው”ብለው መለሱለት።

ሃምሳ ሃምሳ ሆነው ሣሩ ላይ እንዲቀመጡ ለሕዝቡ ይነግሩ ዘንድ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ነገራቸው።

ከዚያም ኢየሱስ አምስቱን እንጀራና ሁለቱን ዓሣ ይዞ ወደ ሰማይ ተመለከተ፣ ስለ ምግቡም እግዚአብሔርን አመሰገነ።

ከዚያም ኢየሱስ እንጀራውንና ዓሣውን ቈረሰ። ለሕዝቡ እንዲያቀርቡም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጣቸው። ደቀ መዛሙርቱ ምግቡን ማደላቸውን ቀጠሉ፣ ከቶም አላለቀም! ሕዝቡ ሁሉ በልተው ጠገቡ።

ከዚያ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ቊርስራሹን ምግብ ሰበሰቡ፣ እርሱም ዐሥራ ሁለት መሶብ ሙሉ ነበር! ምግቡ ሁሉ የመጣው ከአምስቱ እንጀራና ከሁለቱ ዓሣ ነበር።

اطلاعات مربوطه

کلام زندگی - جی آر اِن پیام‌های صوتی انجیل شامل پیام‌هایی بر طبق کتاب مقدس درباره رستگاری و زندگی بصورت یک مسیحی را به هزارن زبان ارائه می‌دهد.

دریافت رایگان - در این قسمت شما می‌توانید تمام پیام‌های اصلی جی آر اِن به چندین زبان، به علاوه تصاویر و دیگر مطالب مرتبط که برای دریافت موجود است را مشاهده کنید.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?