unfoldingWord 10 - ዐሥሩ መቅሠፍቶች

unfoldingWord 10 - ዐሥሩ መቅሠፍቶች

طرح کلی: Exodus 5-10

شماره کتاب: 1210

زبان: Amharic

مخاطبان: General

نوع: Bible Stories & Teac

هدف: Evangelism; Teaching

نقل قول کتاب مقدس: Paraphrase

وضعیت: Approved

اسکریپت ها( سندها)، دستورالعمل های اساسی برای ترجمه و ضبط به زبان های دیگر هستند. آنها باید در صورت لزوم تطبیق داده شوند تا برای هر فرهنگ و زبان مختلف قابل درک و مرتبط باشند. برخی از اصطلاحات و مفاهیم مورد استفاده ممکن است نیاز به توضیح بیشتری داشته باشند، یا جایگزین، یا به طور کامل حذف شوند.

متن کتاب

ሙሴና አሮን ወደ ፈርዖን ሄዱ። “የእስራኤል አምላክ ‘ሕዝቤንልቀቅ !’” ይላሃል አሉት። ፈርዖን አልሰማቸውም። እስራኤላውያን ነጻ ሆነው እንዲሄዱ በማድረግፈንታ ከዚህም የከበደ ሥራ እንዲሠሩ አስገደዳቸው!

ፈርዖን ሕዝቡን አልለቅም ማለቱን ቀጠለ፣ ስለዚህ እግዚአብሔር በግብፅ ላይ ዐሥር መቅሠፍቶችን ላከ። እግዚአብሔር በእነዚህ መቅሠፍቶች በኩል ከፈርዖንና ከግብፅ አማልክት ሁሉ ይልቅ ኃያል መሆኑን ለፈርዖን ዐሳየው።

እግዚአብሔር የዓባይን ውሃ ወደ ደም ለወጠው፣ ነገር ግን ፈርዖን አሁንም እስራኤላውያንን አልለቀቃቸውም።

እግዚአብሔር በግብፅ ሁሉ ላይ እንቁራሪቶችን ላከ። ፈርዖን ሙሴን እንቁራሪቶቹን እንዲያርቅ ለመነው። ሆነም ቀረ ግን እንቁራሪቶቹ ሁሉ ሞቱ። ፈርዖን ልቡን አደነደነና እስራኤላውያንን ከግብፅ እንዲወጡ አልለቀቃቸውም።

ስለዚህ እግዚአብሔር ትንኞችን ላከ። ከዚያም ዝንቦችን ላከ። ፈርዖን ሙሴንና አሮንን ጠራና መቅሠፍቱን ካቆሙ እስራኤላውያን ከግብፅ መሄድ እንደሚችሉ ነገራቸው። ሙሴ በጸለየ ጊዜ እግዚአብሔር ዝንቦችን ሁሉ ከግብፅ አስወገደ። ነገር ግን ፈርዖን ልቡን አደነደነና ሕዝቡን አልለቀቀም።

ቀጥሎ እግዚአብሔር የግብፃውያን ከብቶች ሁሉ ታመው እንዲሞቱ አደረገ። ነገር ግን የፈርዖን ልብ ደነደነና እስራኤላውያንን አልለቀቀም።

ከዚያም እግዚአብሔር በፈርዖን ፊት ዐመድ ወደ ሰማይ እንዲበትን ለሙሴ ነገረው። ዐመዱን በበተነ ጊዜ በግብፃውያን ላይ የሚያም ቊስል ሆነ፣ በእስራኤላውያን ላይ ግን ቊስሉ አልሆነባቸውም። እግዚአብሔር የፈርዖንን ልብ አደነደነ፣ ፈርዖንም እስራኤላውያንን አልለቀቀም።

ከዚያ በኋላ እግዚአብሔር በግብፅ ያለውን አብዛኛውን ቡቃያ ያጠፋና ከቤት ውጪ የነበረውን ማንኛውንም ሰው የገደለ በረዶ ላከ። ፈርዖን ሙሴንና አሮንን ጠርቶ፣ “በድዬአለሁ። መሄድ ትችላላችሁ” ብሎ ነገራቸው። ስለዚህ ሙሴ ጸለየ፣ በረዶውም ከሰማይ መዝነቡን አቆመ።

ነገር ግን ፈርዖን እንደ ገና ኃጢአት ሠራ ልቡንም አደነደነ። እስራኤላውያንን አልለቀቀም።

ስለዚህ እግዚአብሔር በግብፅ ላይ የአንበጣዎችን መንጋ አመጣ። እነዚህ አንበጣዎች በረዶው ያላጠፋውን ሰብል ሁሉ በሉት።

ከዚያም እግዚአብሔር ለሦስት ቀን የቆየ ጨለማ ላከ። ግብፃውያን ከቤቶቻቸው እስከማይወጡ ድረስ በጣም ጨልሞ ነበር። እስራኤላውያን በሚኖሩበት ስፍራ ግን ብርሃን ነበረ።

ከእነዚህ ዘጠኝ መቅሠፍቶች በኋላ እንኳ ፈርዖን አሁንም እስራኤላውያንን አልለቅም አለ። ፈርዖን ስለማይሰማ፣ እግዚአብሔር አንድ የመጨረሻ መቅሠፍት ለመላከ ወሰነ። ይህ የፈርዖንን ዐሳብ ይለውጣል።

اطلاعات مربوطه

کلام زندگی - جی آر اِن پیام‌های صوتی انجیل شامل پیام‌هایی بر طبق کتاب مقدس درباره رستگاری و زندگی بصورت یک مسیحی را به هزارن زبان ارائه می‌دهد.

دریافت رایگان - در این قسمت شما می‌توانید تمام پیام‌های اصلی جی آر اِن به چندین زبان، به علاوه تصاویر و دیگر مطالب مرتبط که برای دریافت موجود است را مشاهده کنید.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons