unfoldingWord 39 - ኢየሱስ ለፍርድ ቀረበ

unfoldingWord 39 - ኢየሱስ ለፍርድ ቀረበ

概要: Matthew 26:57-27:26; Mark 14:53-15:15; Luke 22:54-23:25; John 18:12-19:16

文本編號: 1239

語言: Amharic

聽眾: General

類型/流派: Bible Stories & Teac

目的: Evangelism; Teaching

聖經摘錄: Paraphrase

狀態: Approved

腳本是翻譯和錄製成其他語言的基本指南,它們需要根據實際需要而進行調整以適合不同的文化和語言。某些使用術語和概念可能需要有更多的解釋,甚至要完全更換或省略。

文本文字

አሁን ጊዜው እኩለ ሌሊት ነው። ሊቀ ካህናቱ ይጠይቀው ዘንድ ወታደሮቹ ኢየሱስን ወደ ሊቀ ካህናቱ ቤት ወሰዱት። ጴጥሮስ ራቅ ብሎ ከኋላ ተከተላቸው። ኢየሱስን ወደ ቤቱ ባስገቡት ጊዜ፣ ጴጥሮስ በውጪ ሆኖ እሳት ይሞቅ ነበር።

በቤቱ ውስጥ የአይሁድ መሪዎች ኢየሱስን ለፍርድ አቀረቡት። ስለ እርሱ የዋሹ ብዙ የሐሰት ምስክሮችን አመጡ። ይሁን እንጂ፣ ቃላቸው እርስ በርሱ አልተስማማም፣ ስለዚህ የአይሁድ መሪዎች ኢየሱስ በማንኛውም ነገር በደለኛ መሆኑን ማረጋገጥ አልቻሉም።

በመጨረሻ፣ ሊቀ ካህናቱ ኢየሱስን በቀጥታ ተመለከተውና፣ ንገረን፣ አንተ መሲሑ፣ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህን?" አለው።

ኢየሱስ፣ “እኔ ነኝ፣ እንዲሁም ከእግዚአብሔር ጋር ተቀምጬና ከሰማይ ስመጣ ታያለህ” አለው። ሊቀ ካህናቱ በቊጣ ልብሱን ቀደደና ወደ ሌሎቹ የሃይማኖት መሪዎች፣ “ተጨማሪ ምስክሮች አያስፈልጉም! የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ሲል ሰምታችሁታል። ፍርዳችሁ ምንድን ነው?” ብሎ ጮኸ።

ሁሉም የአይሁድ መሪዎች፣ “መሞት ይገባዋል!” ብለው ለሊቀ ካህናቱ መለሱለት። ከዚያም ኢየሱስን ፊቱን ሸፈኑት፣ ተፉበት፣ መቱት፣ ዘበቱበትም።

ጴጥሮስ ከቤቱ ውጪ በመጠባበቅ ላይ እያለ የቤት ሠራተኛ የሆነች ልጅ ዐየችውና፣ “አንተም ደግሞ ከኢየሱስ ጋር ነበርክ!” አለችው። ጴጥሮስ እርስዋ የተናገረችውን ካደ። ከዚያ በኋላ ሌላዋ የቤት ሠራተኛ ያንኑ ተናገረች፣ ጴጥሮስም እንደገና ካደ። በመጨረሻ ሕዝቡ “ሁለታችሁም ከገሊላ ስለሆናችሁ አንተ ከኢየሱስ ጋር መሆንህን እናውቃለን” አሉ።

ከዚያም ጴጥሮስ፣ “ይህንን ሰው የማውቀው ከሆነ የእግዚአብሔር መርገም በእኔ ላይ ይሁን! ብሎ ማለ። ወዲያውኑ ዶሮ ጮኸ፣ ኢየሱስም ዘወር አለና ጴጥሮስን ተመለከተው።

ጴጥሮስ ሄደና በምሬት አለቀሰ። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ኢየሱስን አሳልፎ የሰጠው ይሁዳ፣ የአይሁድ መሪዎች እንዲሞት በኢየሱስ ላይ እንደ ፈረዱበት ዐየ። ይሁዳ በሐዘን ተሞልቶ ሄደና ራሱን ገደለ።

በነጋታው ማለዳ ላይ የአይሁድ መሪዎች ኢየሱስን ወደ ሮማው ገዥ ወደ ጲላጦስ አመጡት። ጲላጦስ ኢየሱስን ጥፋተኛ ነህ ብሎ ይፈርድበትና በሞት እንዲቀጣ ያደርጋል ብለው ተስፋ አደረጉ። ጲላጦስ ኢየሱስን፣ “የአይሁድ ንጉሥ ነህን?” ብሎ ጠየቀው።

ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰለት፣ “አንተ አልህ፣ ነገር ግን መንግሥቴ ምድራዊ መንግሥት አይደለችም። እንደዚያ ብትሆን ኖሮ፣ አገልጋዮቼ ይዋጉልኝ ነበር። ስለ እግዚአብሔር እውነቱን ለመናገር ወደ ምድር መጥቼአለሁ። እውነትን የሚወድ ሁሉ እኔን ይሰማኛል።” ጲላጦስ፣ “እውነት ምንድን ነው?” አለ።

ጲላጦስ ከኢየሱስ ጋር ከተነጋገረ በኋላ ወደ ሕዝቡ ወጣና፣ “በዚህ ሰው ላይ ምንም በደል አላገኘሁበትም” አለ። የአይሁድ መሪዎችና ሕዝቡ ግን፣ “ስቀለው!” ብለው ጮኹ። ጲላጦስ፣ “በደለኛ አይደለም” ብሎ መለሰላቸው። እነርሱ ግን የበለጠ ጮኹ። ከዚያም ጲላጦስ ለሦስተኛ ጊዜ፣ “በደል የለበትም!” አለ።

ጲላጦስ ሕዝቡ መረበሽ ይጀምራሉ ብሎ ፈራ፣ ስለዚህ ኢየሱስን እንዲሰቅሉት ወታደሮቹን አዘዘ። የሮማ ወታደሮች ኢየሱስን ገረፉትና ቀይ ልብስ አለበሱት፣ እንዲሁም የሾኽ አክሊል በራሱ ላይ አደረጉ። ከዚያም፣ “እነሆ፣ የአይሁድ ንጉሥ!” በማለት ዘበቱበት።

相關信息

生命之道 - 環球錄音網擁有用數以千計的語言去錄製的福音信息,內容包括一些有關救恩和基督徒樣式的聖經信息。

免費下載 - 免費下載傳教及發展教會組織所用的錄音、圖片、文本和其他相關資料。內容包括聖經故事與傳教課程,并已被翻譯成上千種語言。

環球錄音網音頻圖書館 - 提供mp3,CD和磁帶形式的傳播福音和基本的宣教材料,適宜人們的需要和文化。錄音材料的形式多樣,包括簡單的聖經故事,福音信息,經文朗誦和歌曲。

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons