unfoldingWord 24 - ዮሐንስ ኢየሱስን አጠመቀ

unfoldingWord 24 - ዮሐንስ ኢየሱስን አጠመቀ

概要: Matthew 3; Mark 1; Luke 3; John 1:15-37

文本编号: 1224

语言: Amharic

听众: General

类型/流派: Bible Stories & Teac

目的: Evangelism; Teaching

圣经摘录: Paraphrase

状态: Approved

脚本是翻译和录制成其他语言的基本指南,它们需要根据实际需要而进行调整以适合不同的文化和语言。某些使用术语和概念可能需要有更多的解释,甚至要完全更换或省略。

文本正文

የዘካርያስና የኤልሳቤጥ ልጅ ዮሐንስ አደገና ነቢይ ሆነ። በምድረ በዳ ኖረ፣ የበረሐ ማርና አንበጣ ተመገበ፣ ከግመል ፀጉር የተሠራ ልብስም ለበሰ።

ብዙ ሕዝብ ዮሐንስን ለመስማት ወደ ምድረ በዳ መጡ። እርሱም፣ “የእግዚአብሔር መንግሥት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ” በማለት ሰበከላቸው።

ሕዝቡ የዮሐንስን መልእክት በሰሙ ጊዜ፣ አብዛኞቻቸው ኃጢአታቸውን ተናዘዙ፣ ዮሐንስም አጠመቃቸው። ብዙ የሃይማኖት መሪዎች ደግሞ በዮሐንስ ሊጠመቁ መጡ፣ ነገር ግን ንስሐ አልገቡም ወይም ኃጢአታቸውን አልተናዘዙም።

ዮሐንስ ለሃይማኖት መሪዎቹ እንዲህ አላቸው፣ “እናንተ መርዛማ እባቦች! ንስሐ ግቡና ድርጊታችሁን ለውጡ። መልካም ፍሬ የማያፈራ ዛፍ ሁሉ ይቈረጥና ወደ እሳት ይጣላል።” ዮሐንስ ነቢያት “እነሆ፣ መንገድህን የሚያዘጋጅ መልእክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ።” በማለት የተናገሩትን ፈጽመ።

አንዳንድ አይሁዶች መሲሕ ስለ መሆኑ ዮሐንስን ጠየቁት። ዮሐንስ እንዲህ ብሎ መለሰ፣ “እኔ መሲሑ አይደለሁም፣ ነገር ግን ከእኔ በኋላ የሚመጣ አንድ ሰው አለ። የጫማውን ማሰሪያ ልፈታ እንኳ የማይገባኝ በጣም ታላቅ ነው።”

በቀጣዩ ቀን፣ ኢየሱስ በዮሐንስ ለመጠመቅ መጣ። ዮሐንስ ባየው ጊዜ፣ “ተመልከቱ! እነሆ፣ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ” አለ።

ዮሐንስ ኢየሱስን፣ “እኔ አንተን ለማጥመቅ ተገቢ ሰው አይደለሁም። በዚህ ፈንታ አንተ እኔን ማጥመቅ አለብህ እንጂ” አለው። ኢየሱስ ግን፣ “መደረግ ያለበት ትክክለኛ ነገር ነውና አንተ እኔን ማጥመቅ ይገባሃል” አለ። ስለዚህ ኢየሱስ ከቶ ኃጢአት ባይሠራም እንኳ ዮሐንስ ኢየሱስን አጠመቀው።

ኢየሱስ ከተጠመቀ በኋላ ከውኃው እንደ ወጣ፣ የእግዚአብሔር መንፈስ በርግብ አምሳል ታየና ወርዶ በእርሱ ላይ ዐረፈ። በዚሁ ጊዜ የእግዚአብሔር ድምፅ ከሰማይ፣ “አንተ እኔ የምወድህ ልጄ ነህ፣ በአንተም በጣም ደስ ብሎኛል” ብሎ ተናገረ።

እግዚአብሔር ለዮሐንስ፣ “መንፈስ ቅዱስ ይወርድና አንተ በምታጠምቀው ሰው ላይ ያርፋል። ሰውዬው የእግዚአብሔር ልጅ ነው” ብሎ ተናግሮት ነበር። አንድ አምላክ ብቻ አለ። ነገር ግን ዮሐንስ ኢየሱስን ባጠመቀው ጊዜ፣ እግዚአብሔር አብ ሲናገር ሰማ፣ እግዚአብሔር ወልድን ዐየ፣ እርሱም ኢየሱስ ነው፣ እንዲሁም መንፈስ ቅዱስን ዐየ።

相关信息

人生箴言 - GRN提供几千种语言的福音音频信息,包含圣经信息,救赎和基督徒生活。

免费下载 - 免费下载传福音及发展教会所用的录音、图片、文本和其他相关资料。内容包括福音与圣经故事,并已被翻译成上千种语言。

环球录音网音频图书馆 - Mp3,CD和磁带格式的福音材料和圣经教学材料,满足人们不同文化的需求。录音材料的形式多样,包括简单的圣经故事,福音信息,经文朗诵和歌曲。

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons