unfoldingWord 05 - የተስፋው ልጅ

unfoldingWord 05 - የተስፋው ልጅ

概要: Genesis 16-22

文本编号: 1205

语言: Amharic

听众: General

类型/流派: Bible Stories & Teac

目的: Evangelism; Teaching

圣经摘录: Paraphrase

状态: Approved

脚本是翻译和录制成其他语言的基本指南,它们需要根据实际需要而进行调整以适合不同的文化和语言。某些使用术语和概念可能需要有更多的解释,甚至要完全更换或省略。

文本正文

ከዐሥር ዓመታት በኋላ አብራምና ሦራ ከነዓን ደረሱ፣ እስከዚህ ድረስ ልጅ አልነበራቸውም። ስለዚህም የአብራም ሚስት ሦራ እንዲህ አለችው “እግዚአብሔር ልጆች እንዳይኖሩኝ ስለከለከለኝና እኔም ስላረጀሁ አገልጋዬ አጋር ይህችትልህ አግባት ለኔም ልጅ ትውለድለኝ” አለችው።

ስለሆነም አብራም አጋርን አገባት። አጋርም ወንድ ልጅ ወለደች። አብራምም “እስማኤል” ሲል ስም አወጣለት፤ ይሁን እንጂ ሦራ በአጋር ቀናችባት፤ እስማኤል ዐሥራ ሦስት ዓመት ሲሆነው እግዚአብሔር አብራምን እንዲህ አለው።

እግዚአብሔርም አብራምን“እኔ ኤልሻዳይ አምላክ ነኝ ካንተ ጋር ኪዳን እገባለሁ” አለው። አብራምምበግምባሩ መሬት ላይ ተደፋ እግዚአብሔርም አብራምንአለው “አንተ የብዙ ሕዝቦች አባት ትሆናለህ። የከነዓንን ምድር ለአንተና ለዘሮችህ ርስት አድርጌ እሰጣችኋለሁ እኔም ለዘላለም አምላካቸው እሆናለሁ አንተም በቤተ ሰብህ የሚገኘውን ወንድ ሁሉ ግረዘው” አለው።

እግዚአብሔርም “ሚስትህ ሦራ ወንድ ልጅ ትወልዳለች እርሱም የተስፋው ልጅ ይሆናል ስሙን ይስሐቅ ብለህ ትጠራዋለህ ኪዳኔንም ከእርሱ ጋር አደርጋለሁ። እርሱም ታላቅ ሕዝብ ይሆናል። እስማኤልንም ታላቅ ሕዝብ አደርገዋለሁ፤ ይሁን እንጂ ኪዳኔ ከይስሐቅ ጋር ይሆናል” አለው። እግዚአብሔርም የአብራምን ስም “አብርሃም” ሲል ለወጠለት ትርጓሜውም “የብዙዎች አባት” ማለት ነው። እግዚአብሔር የሦራንም ስም “ሣራ” ሲል ለወጠላት ትርጓሜውም “የብዙዎች እናት” ማለት ነው።

በዚያኑ ዕለት አብርሃም በቤተ ሰቡ የሚኙትን ወንዶች ሁሉ ገረዘ። ከዓመት በኋላ አብርሃም 100 ዓመት ሲሆነውና ሣራ 99 ዓመት በሆናት ጊዜ ለአብርሃም ወንድ ልጅ ወለደችለት እግዚአብሔርም እንዳላቸው “ይስሐቅ” ሲሉ ስም አወጡለት።

ይስሐቅ ወጣት በሆነ ጊዜ እግዚአብሔር የአብርሃምን እምነት እንዲህ ሲል ፈተነው፤ “አንዱን ልጅህን ውሰድና ለኔ መሥዋዕት አድርገህ አቅርብልኝ” አለው፤ እንደ ገና አብርሃም እግዚአብሔርን ታዘዘና ልጁን ሊሠዋው አዘጋጀ።

አብርሃምና ይስሐቅ መሥዋዕት ወደሚደረግበት ስፍራ መጓዝ እንደ ጀመሩ ይስሐቅ አባቱን “አባቴ ሆይ ለመሥዋዕት ማቅረቢያ እንጨቱ ይኸውና በጉ ግን የታለ?” ሲል ጠየቀ። አብርሃምም “ልጄ ሆይ የመሥዋዕቱን በግ እግዚአብሔር ያዘጋጃል” ሲል መለሰለት።

ወደ መሥዋዕት ማቅረቢያ ቦታ እንደ ደረሱ አብርሃም ልጁን ይስሐቅን አስሮ በመሠዊያው ላይ አጋደመው። አብርሃምም ልጁን ለማረድ እጁን ዘርግቶ ቢላዋውን አነሣ፤ እግዚአብሔር “ተው በልጁ ላይ ምንም ጉዳት አታድርስበት እንደምትፈራኝና አንድያ ልጅህን ሳስተህ ለኔ እንዳልከለከልከኝ አሁን አውቄአለሁ አለው።

በአቅራቢያው አብርሃም በቊጥቋጦ ውስጥ የታሰረ በግ አየ። እግዚአብሔር በይስሐቅ ፋንታ ለመሥዋዕት የሚሆን በግ አዘጋጅቶ ነበር። አብርሃምም በደስታ በጉን መሥዋዕት አድርጎ አቀረበ።

እግዚአብሔርም አብርሃምን አለው፣ “አንድያ ልጅህን ሳይቀር ያለህን ሁሉ ልትሰጠኝ ፍቃደኛ ነበርህና ልባርክህ ቃል እገባለሁ። ዘሮችህ ከሰማይ ክዋክብት ይልቅ ይበዛሉ እኔን ስለ ታዘዝከኝ የዓለም ሕዝቦች ሁሉ ባንተ ይባረካሉ።”

相关信息

人生箴言 - GRN提供几千种语言的福音音频信息,包含圣经信息,救赎和基督徒生活。

免费下载 - 免费下载传福音及发展教会所用的录音、图片、文本和其他相关资料。内容包括福音与圣经故事,并已被翻译成上千种语言。

环球录音网音频图书馆 - Mp3,CD和磁带格式的福音材料和圣经教学材料,满足人们不同文化的需求。录音材料的形式多样,包括简单的圣经故事,福音信息,经文朗诵和歌曲。

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons