unfoldingWord 37 - ኢየሱስ አልዓዛርን ከሞት አስነሣ

unfoldingWord 37 - ኢየሱስ አልዓዛርን ከሞት አስነሣ

Đề cương: John 11:1-46

Số kịch bản: 1237

ngôn ngữ: Amharic

Khán giả: General

Thể loại: Bible Stories & Teac

Mục đích: Evangelism; Teaching

Trích dẫn Kinh Thánh: Paraphrase

Trạng thái: Approved

Bản văn này là một hướng dẫn cơ bản cho dịch và thu âm trong các ngôn ngữ khác. Nó phải được thích nghi với nền văn hóa và ngôn ngữ để làm cho nó phù hợp với từng khu vực, nơi nó được sử dụng khác nhau. Một số thuật ngữ và khái niệm được sử dụng có thể cần một lời giải thích đầy đủ hơn hoặc thậm chí bị bỏ qua trong các nền văn hóa khác nhau.

Kịch bản

አንድ ቀን ኢየሱስ አልዓዛር በጣም ታሞአል የሚል መልእክት ደረሰው። አልዓዛርና ሁለቱ እኅቶቹ ማርያምና ማርታ የኢየሱስ የቅርብ ወዳጆች ነበሩ። ኢየሱስ ይህንን ወሬ በሰማ ጊዜ፣ “ይህ ሕመም ለእግዚአብሔር ክብር ነው እንጂ ለሞት አይደለም” አለ። ኢየሱስ ወዳጆቹን ይወዳቸው ነበር፣ ነገር ግን ለሁለት ቀናት በነበረበት ስፍራ ቆየ።

ሁለቱ ቀናት ካለፉ በኋላ፣ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን፣ “ወደ ይሁዳ እንሂድ” አላቸው። “ነገር ግን መምህር ሆይ፣”ልክ ከጥቂት ጊዜ በፊት በዚያ ያሉት ሕዝብ ሊገድሉህ ይፈልጉ ነበር!" ብለው ደቀ መዛሙርቱ መለሱለት። ኢየሱስ፣ “ወዳጃችን አልዓዛር አንቀላፍቶአል፣ ከእንቅልፉ ላስነሣው እሄዳለሁ” አላቸው።

የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት፣ “ጌታ ሆይ፣ አልዓዛር ተኝቶስ ከሆነ፣ ይድናል” ብለው መለሱለት። በዚያን ጊዜ ኢየሱስ በግልጽ ነገራቸው፣ “አልዓዛር ሞቶአል። እናንተ በእኔ ታምኑ ዘንድ እዚያ ባለመኖሬ ደስ ብሎኛል።”

ኢየሱስ አልዓዛር ወደ ተወለደበት ከተማ በደረሰ ጊዜ፣ አልዓዛር ከሞተ አራት ቀን ሆኖት ነበር። ማርታ ኢየሱስን ልትገናኘው ወጣችና እንዲህ አለች፣ “ጌታ ሆይ፣ አንተ እዚህ ብትኖር ኖሮ ወንድሜ አይሞትም ነበር። ነገር ግን እግዚአብሔር የምትለምነውን ሁሉ እንደሚሰጥህ አምናለሁ።”

ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰላት፣ “እኔ ትንሣኤና ሕይወት ነኝ። በእኔ የሚያምን ሁሉ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል። በእኔ የሚያምን ሁሉ ከቶ አይሞትም። ይህን ታምኛለሽን? ማርታ፣”አዎን፣ ጌታ ሆይ! አንተ መሲሑ፣ የእግዚአብሔር ልጅ መሆንህን አምናለሁ" ብላ መለሰችለት።

ከዚያም ማርያም መጣች። በኢየሱስ እግር ወደቀችና፣ “ጌታ ሆይ፣ አንተ በዚህ ኖረህ ብትሆን ኖሮ ወንድሜ ባልሞተም ነበር” አለች። ኢየሱስ፣ “አልዓዛርን ወዴት ነው ያኖራችሁት?” ብሎ ጠየቃቸው። “በመቃብር ነው። ናና እይ” ብለው ነገሩት። ከዚያም ኢየሱስ አለቀሰ።

መቃብሩ ዋሻ ነበር፣ ድንጋይም ተገጥሞበት ነበር። ኢየሱስ ወደ መቃብሩ በደረሰ ጊዜ ድንጋዩን አንከባሉት" ብሎ ነገራቸው። ነገር ግን ማርታ፣ “ከሞተ አራት ቀን ሆኖታል። አሁን ይሸታል” አለችው።

ኢየሱስ፣ “በእኔ ብታምኚስ የእግዚአብሔርን ክብር እንድታዪ አልነገርኩሽምን?” አላት። ስለዚህ ድንጋዩን አንከባለሉት።

ከዚያ በኋላ ኢየሱስ ወደ ላይ ተመለከተና፣ “አባት ሆይ፣ ስለምትሰማኝ አመሰግንሃለሁ። አንተ ሁልጊዜ እንደምትሰማኝ ዐውቃለሁ፣ ነገር ግን አንተ እንደ ላክኸኝ ያምኑ ዘንድ እዚህ ስለ ቆሙት ስለ እነዚህ ሰዎች ሁሉ ይህን እላለሁ” አለ። ከዚያም ኢየሱስ፣ “አልዓዛር ሆይ፣ ወደ ውጭ ና!” ብሎ ጮኸ።

ስለዚህ አልዓዛር ወጣ! በከፈን እንደ ተገነዘ ነበር። ኢየሱስም፣ “ፍቱትና ይሂድ ተዉት!” አላቸው። ከአይሁድ ብዙዎች በዚህ ተአምር ምክንያት በኢየሱስ አመኑ።

ነገር ግን የአይሁድ የሃይማኖት መሪዎች ቀኑ፣ ስለዚህ ኢየሱስንና አልዓዛርን እንዴት መግደል እንዳለባቸው ለማቀድ በአንድ ላይ ተሰበሰቡ።

Thông tin liên quant

Lời Sự Sống - GRN có lưu trữ hàng ngàn thu âm của các lời dạy Phúc Âm bằng các thứ tiếng khác nhau bao gồm từ những thông điệp cơ bản từ Kinh thánh

Tài liệu miễn phí - Tại đây bạn có thể tìm thấy các thông điệp chính của GRN bằng các thứ tiếng khác nhau bao gổm cả hình ảnh và các tài liệu khác có liên quan có thể tải xuống được

Thư viện âm thanh của GRN - Các tài liệu giảng dạy Kinh Thánh cơ bản và nâng cao phù hợp với nhu cầu và văn hóa của mọi người, đa dạng về cả hình thức và phong cách

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?