unfoldingWord 47 - ጳውሎስና ሲላስ በፊልጵስዩስ

unfoldingWord 47 - ጳውሎስና ሲላስ በፊልጵስዩስ

Đề cương: Acts 16:11-40

Số kịch bản: 1247

ngôn ngữ: Amharic

Khán giả: General

Thể loại: Bible Stories & Teac

Mục đích: Evangelism; Teaching

Trích dẫn Kinh Thánh: Paraphrase

Trạng thái: Approved

Bản văn này là một hướng dẫn cơ bản cho dịch và thu âm trong các ngôn ngữ khác. Nó phải được thích nghi với nền văn hóa và ngôn ngữ để làm cho nó phù hợp với từng khu vực, nơi nó được sử dụng khác nhau. Một số thuật ngữ và khái niệm được sử dụng có thể cần một lời giải thích đầy đủ hơn hoặc thậm chí bị bỏ qua trong các nền văn hóa khác nhau.

Kịch bản

ሳውል በሮማ የንጉሠ ነገሥት ግዛት ሁሉ በሚጓዝበት ጊዜ፣ ሮማዊ ስሙን “ጳውሎስ”ን መጠቀም ጀመረ። አንድ ቀን ጳውሎስና ጓደኛው ሲላስ ስለ ኢየሱስ የሚናገረውን የምሥራች ሊያውጁ ወደ ፊልጵስዩስ ከተማ ሄዱ። ሰዎች ሊጸልዩ ወደ ተሰበሰቡበት ከከተማይቱ ውጭ በወንዙ አጠገብ ወዳለ ስፍራ ሄዱ። በዚያ ነጋዴ የነበረች ልድያ የሚሉአት አንዲት ሴት አገኙ። እርስዋ እግዚአብሔርን ትወድና ታመልክ ነበር።

ስለ ኢየሱስ የሚነገረውን መልእክት እንድታምን እግዚአብሔር የልድያን ልብ ከፈተላት፤ እርስዋና ቤተ ሰብዋ ተጠመቁ፣ በቤትዋ እንዲኖሩ ጳውሎስንና ሲላስን ጋበዘቻቸው፣ ስለዚህ እነርሱ ከእርስዋና ከቤተ ሰብዋ ጋር ኖሩ።

ጳውሎስና ሲላስ ብዙ ጊዜ በጸሎት ስፍራ ከሰዎች ጋር ይገናኙ ነበር። በየዕለቱ ወደዚያ ሲሄዱ ጋኔን የያዛት አንዲት ባሪያ ልጃገረድ ትከተላቸው ነበር። እርሷም በዚህ ጋኔን አማካይነት ስለ መጪው ጊዜ ለሰዎች ትተነብይላቸው ነበር፣ ስለዚህ በጥንቈላ ለጌቶችዋ ብዙ ገንዘብ ታስገኝ ነበር።

ባሪያዪቱ ልጃገረድ እነርሱ ሲዘዋወሩ እየተከተለቻቸው፣ “እነዚህ ሰዎች የልዑል እግዚአብሔር አገልጋዮች ናቸው። የመዳንን መንገድ ይነግሩአችኋል!” በማለት መጮህዋን ቀጠለች። ጳውሎስ እስኪቈጣ ድረስ ይህንን ደጋግማ አደረገች።

በመጨረሻም አንድ ቀን ባሪያዪቱ ልጃገረድ መጮኽ በጀመረች ጊዜ ጳውሎስ ወደ እርስዋ ዘወር አለና በእርስዋ የነበረውን ጋኔን፣ “በኢየሱስ ስም፣ ከእርስዋ ውጣ” አለው። ወዲያውኑ ጋኔኑ ለቀቃት።

የባሪያዪቱ ልጃገረድ ጌቶች የነበሩት ሰዎች በጣም ተቈጡ! ያለ ጋኔኑ ባሪያዪቱ ልጅ ስለ ሰዎች መጪ ጊዜ መናገር እንደማትችል ዐወቁ። ይህም ሰዎች የሚደርስባቸውን ነገር ትነግራቸው ዘንድ ስለማትችል ለጌቶችዋ ገንዘብ አይከፍሉም ማለት ነው።

ስለዚህ የባሪያዪቱ ልጃገረድ ጌቶች ጳውሎስንና ሲላስን ወደ ሮማ ባለ ሥልጣናት ወሰዱአቸው፣ እነርሱም ደብድበው ወደ እስር ቤት ጣሉአቸው።

እነርሱም ጳውሎስንና ሲላስን በእስር ቤት ውስጠኛ ክፍል አሰሩአቸው እግሮቻቸውን እንኳ ከግንድ ጋር አሰሩአቸው። ሆኖም ግን እከለ ሌሊት ላይ ለእግዚአብሔር የምስጋና መዝሙር ዘመሩ።

በድንገት ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ ሆነ! የእስር ቤቱ በሮች ሁሉ ወለል ብለው ተከፈቱ፣ የእስረኞቹ ሁሉ ሰንሰለቶችም ረገፉ።

የእስር ቤቱ ጠባቂ ከእንቅልፉ ነቃ፣ የእስር ቤቱ በሮች ሁሉ መከፈታቸውን ባየ ጊዜ ፈራ! እስረኞቹ ሁሉ ያመለጡ መሰለው፣ ስለዚህ ራሱን ለመግደል ዐሰበ። (እስረኞቹ እንዲያመልጡ ካደረገ የሮማ ባለ ሥልጣናት እንደሚገድሉት ዐወቀ።) ነገር ግን ጳውሎስ ዐየውና፣ “ተው! ራስህን አትጕዳ። ሁላችንም እዚህ አለን” ብሎ ጮኸበት።

የእስር ቤቱ ጠባቂ ወደ ጳውሎስና ሲላስ እየመጣ እያለ ተንቀጠቀጠና፣ “እድን ዘንድ ምን ላድርግ?” ብሎ ጠየቀ። ጳውሎስ፣ “በጌታ በኢየሱስ እመን፣ አንተና ቤተ ሰዎችህ ትድናላችሁ” ብሎ መለሰለት። ከዚያም የእስር ቤት ጠባቂው ጳውሎስንና ሲላስን ወደ ቤቱ ወሰዳቸውና ቊስላቸውን አጠበላቸው። ጳውሎስ በቤቱ ለነበሩት ሁሉ ስለ ኢየሱስ የሚናገረውን የምሥራች ሰበከላቸው።

የእስር ቤት ጠባቂውና መላው ቤተ ሰቡ በኢየሱስ አምነው ተጠመቁ። ከዚያም የእስር ቤት ጠባቂው ለጳውሎስና ለሲላስ ምግብ አቀረበላቸውና በአንድነት ደስ አላቸው፡

በማግስቱ የፊልጵስዩስ መሪዎች ጳውሎስና ሲላስን ከእስር ቤት ፈቱአቸውና ከፊልጵስዩስ እንዲሄዱ ጠየቁአቸው። ጳውሎስና ሲላስ ልድያንና አንዳንድ ሌሎች ወዳጆችን ጐበኙና ከተማይቱን ለቀው ሄዱ። ስለ ኢየሱስ የሚናገረው የምሥራች መስፋፋቱን ቀጠለ ቤተ ክርስቲያንም ማደግዋን ቀጠለች።

ጳውሎስና ሌሎች ክርስቲያን መሪዎች ስለ ኢየሱስ የሚናገረውን የምሥራች እየሰበኩና እያስተማሩ ወደ ብዙ ከተሞች ተጓዙ። ደግሞም በአብያተ ክርስቲያናቱ ላሉ አማኞች ሊያበረታቱአቸውና ሊያስተምሩአቸው ብዙ መልእክቶችን ጻፉላቸው። ከእነዚህ መልእክቶች አንዳንዶቹ በመጽሐፍ ቅዱስ ያሉት መጻሕፍት ሆኑ።

Thông tin liên quant

Lời Sự Sống - GRN có lưu trữ hàng ngàn thu âm của các lời dạy Phúc Âm bằng các thứ tiếng khác nhau bao gồm từ những thông điệp cơ bản từ Kinh thánh

Tài liệu miễn phí - Tại đây bạn có thể tìm thấy các thông điệp chính của GRN bằng các thứ tiếng khác nhau bao gổm cả hình ảnh và các tài liệu khác có liên quan có thể tải xuống được

Thư viện âm thanh của GRN - Các tài liệu giảng dạy Kinh Thánh cơ bản và nâng cao phù hợp với nhu cầu và văn hóa của mọi người, đa dạng về cả hình thức và phong cách

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons