unfoldingWord 28 - ባለ ጠጋው ወጣት
![unfoldingWord 28 - ባለ ጠጋው ወጣት](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_19_05.jpg)
Đề cương: Matthew 19:16-30; Mark 10:17-31; Luke 18:18-30
Số kịch bản: 1228
ngôn ngữ: Amharic
Khán giả: General
Thể loại: Bible Stories & Teac
Mục đích: Evangelism; Teaching
Trích dẫn Kinh Thánh: Paraphrase
Trạng thái: Approved
Bản văn này là một hướng dẫn cơ bản cho dịch và thu âm trong các ngôn ngữ khác. Nó phải được thích nghi với nền văn hóa và ngôn ngữ để làm cho nó phù hợp với từng khu vực, nơi nó được sử dụng khác nhau. Một số thuật ngữ và khái niệm được sử dụng có thể cần một lời giải thích đầy đủ hơn hoặc thậm chí bị bỏ qua trong các nền văn hóa khác nhau.
Kịch bản
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_19_01.jpg)
አንድ ቀንአንድ ባለጠጋወጣት ወደ ኢየሱስ መጣና፣ “ቸር መምህር፣ የዘላለምን ሕይወት እንድወርስ ምን ላድርግ?” ብሎ ጠየቀው። ኢየሱስ፣ “ስለ ምን ‘ቸር’ ትለኛለህ? ቸርአንድ ብቻአለ፣ እርሱም እግዚአብሔር ነው።ነገር ግንአንተ የዘላለም ሕይወት እንዲኖርህ ከፈለግህ ለእግዚአብሔር ሕግታዘዝ” አለው።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_19_02.jpg)
“የትኞቹን ልታዘዝ?” ብሎ ጠየቀው። ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰለት፣ “አትግደል። አታመንዝር። አትስረቅ። አትዋሽ። አባትህንና እናትህን አክብር፣ ባልጀራህንምእንደ ራስህ ውደድ።”
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_19_03.jpg)
ነገር ግን ወጣቱ፣ “ከልጅነቴጀምሮ እነዚህንሕጎች ሁሉ ፈጽሜአለሁ። ለዘላለም ለመኖርሌላስ ምን ማድረግ ያስፈልገኛል?” አለ። ኢየሱስ ዐየውና ወደደው።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_19_04.jpg)
ኢየሱስ፣ “ፍጹም ለመሆን ብትፈልግ፣ ያለህን ንብረት ሁሉሽጥና ገንዘቡን ለድሆች ስጥ፣ በሰማይም መዝገብ ታገኛለህ። ከዚያም በኋላ ናና ተከተለኝ” ብሎመለሰለት።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_19_05.jpg)
ወጣቱ፣ ኢየሱስ የተናገረውን በሰማ ጊዜ፣ በጣም ባለ ጠጋ ነበርና ያለውን ነገር ሁሉ መስጠት ስላልፈለገ በጣም ዐዘነ። ከኢየሱስ ፊቱን አዞረና ሄደ።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_19_06.jpg)
በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን እንዲህ አላቸው፣ “ለባለ ጠጎች ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት እጅግ አስቸጋሪ ነው! አዎ፣ ባለ ጠጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ይልቅ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢያልፍ ይቀላል።”
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_19_07.jpg)
ደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስ የተናገረውን በሰሙ ጊዜ ደነገጡና፣ “ታዲያ ማን ሊድን ይችላል?” አሉ።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_19_08.jpg)
ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ተመለከተና፣ “ይህ በሰው ዘንድ አይቻልም፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ሁሉ ይቻላል” አለ።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_19_09.jpg)
ጴጥሮስ ኢየሱስን፣ “እኛ ሁሉን ትተን ተከተልንህ። ዋጋችን ምን ይሆን?” አለው።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_19_10.jpg)
ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰለት፣ “ስለ እኔ ቤቶችን፣ ወንድሞችን፣ እኅቶችን፣ አባትን፣ እናትን ወይም ንብረትን የተወ ሁሉ መቶ እጥፍ ይቀበላል የዘላለምንም ሕይወት ይወርሳል። ነገር ግን ፊተኞች የሆኑ ብዙዎች ኋለኞች፣ ኋለኞችም የሆኑ ብዙዎች ፊተኞች ይሆናሉ።”