unfoldingWord 22 - የዮሐንስ መወለድ

unfoldingWord 22 - የዮሐንስ መወለድ

Balangkas: Luke 1

Bilang ng Talata: 1222

Wika: Amharic

Tagapakinig: General

Klase: Bible Stories & Teac

Layunin: Evangelism; Teaching

Kawikaan mula sa Bibliya: Paraphrase

Katayuan: Approved

Ang mga script ay panimulang gabay para sa pagsasalin at pagre-record sa ibat-ibang wika.Ang mga ito ay ay dapat na angkupin kung kinakailangan para maunawaan at makabuluhan sa bawat kultura at wika. Ilang termino at konsepto na ginamit ay maaaring gamitin para maipaliwanag o maaari di na palitan o tanggalin ng ganap.

Salita ng Talata

አስቀድሞ እግዚአብሔር በመላእክቱና በነቢያቱ በኩል ለሕዝቡ ተናግሮ ነበር። ነገር ግን ለእነርሱ ያልተናገረባቸው 400 ዓመታት አለፉ። በድንገት አንድ መልአክ ዘካርያስ ተብሎ ወደሚጠራ ሽማግሌ ካህን ከእግዚአብሔር ዘንድ መልእክት ይዞ መጣ። ዘካርያስና ሚስቱ ኤልሳቤጥ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች ነበሩ፣ ነገር ግን እርስዋ ልጆችን መውለድ አልቻለችም ነበር።

መልአኩ ዘካርያስን አለው፣ “ሚስትህ ወንድ ልጅ ትወልዳለች። ዮሐንስ ብለህ ተጠራዋለህ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ ይሞላል፣ ሕዝቡንም ለመሲሑ ያዘጋጃል!” ዘካርያስ፣ “ሚስቴና እኔ ልጆችን ለመውለድ በጣም አርጅተናል! ይህ እንደሚሆን እንዴት ዐውቃለሁ?” ብሎ መለሰ።

መልአኩ ለዘካርያስ እንዲህ ብሎ መለሰለት፣ ይህን የምሥራች እንዳመጣላችሁ እግዚአብሔር ላከኝ። ስላላመንከኝ፣ ልጁ እስኪወለድ ድረስ መናገር አትችልም።" ወዲያኑ ዘካርያስ መናገር አልቻለም። ከዚያ በኋላ መልአኩ ከዘካርያስ ተለየ። ዘካርያስም ወደ ቤት ተመለሰ ሚስቱም ፀነሰች።

ኤልሳቤጥ የስድስት ወር ነፍሰ ጡር በነበረች ጊዜ፣ ያው መልአክ በድንገት ስምዋ ማርያም ለተባለ ለኤልሳቤጥ ዘመድ ተገለጠ። እርስዋ ድንግል ነበረችና ልታገባ ዮሴፍ ለተባለ ሰው ታጭታ ነበር። መልአኩ፣ “ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ። ስሙን ኢየሱስ ትዪዋለሽ። እርሱም የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ይባላል ለዘላለምም ገዥ ይሆናል” አለ።

ማርያም “እኔ ድንግል ስለ ሆንኩ፣ ይህ እንዴት ይሆናል?” ብላ መለሰች። መልአኩ እንዲህ ብሎ አብራራ፣ “መንፈስ ቅዱስ ወደ አንቺ ይመጣል፣ የልዑል ኃይል ይጸልልሻል። ስለዚህ ልጁ ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይሆናል።” ማርያም አመነች መልአኩ ያለውንም ተቀበለች።

መልአኩ ለማርያም ከተናገረ በኋላ ወዲያወኑ፣ ሄደችና ኤልሳቤጥን ጐበኘቻት። ኤልሳቤጥ የማርያምን ሰላምታ እንደ ሰማች፣ የኤልሳቤጥ ልጅ በሆዷ ውስጥ ዘለለ። ሴቶቹ እግዚአብሔር ስላደረገላቸው ነገር አብረው ሐሤት አደረጉ። ማርያም ኤልሳቤጥን ለሦስት ወራት ከጐበኘቻት በኋላ፣ ማርያም ወደ ቤትዋ ተመለሰች።

ኤልሳቤጥ ወንድ ልጅዋን ከወለደች በኋላ፣ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ መልአኩ እንዳዘዘው ሕፃኑን ዮሐንስ ብለው ሰየሙት። በዚያን ጊዜ እግዚአብሔር ለዘካርያስ እንደ ገና እንዲናገር ፈቀደለት። ዘካርያስ እንዲህ አለ፣ “ሕዝቡን ዐስቦአልና እግዚአብሔር ይመስገን! አንተም ልጄ፣ ለኃጢአታቸው ይቅርታ መቀበል እንዴት እንደሚችሉ ለሕዝቡ የምትናገር የልዑል እግዚአብሔር ነቢይ ትባላለህ!”

Katulad na kaalaman

Salita ng Buhay - Ang GRN ay mayroong mensahe sa audio sa libo-libong wika na naglalaman ng mensahe base sa Bibliya tungkul sa kaligtasan at Kristyanong pamumuhay.

Libreng mga download - Dito ay matatagpuan ang lahat ng pangunahing scripts mensahe ng GRN sa ibat-ibang wika, at mga larawan at iba pang katulad na materyales, ay maaari ng i-download.

Ang GRN Aklatang Audio - Pag-eebanghelyo at panimulang kagamitan ng katuruang Bibliya na angkop sa mga pangangailangan at kultura ng mga tao sa isang iba't ibang estilo at mga format.

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?