unfoldingWord 26 - ኢየሱስ አገልግሎቱን ጀመረ

unfoldingWord 26 - ኢየሱስ አገልግሎቱን ጀመረ

Balangkas: Matthew 4:12-25; Mark 1-3; Luke 4

Bilang ng Talata: 1226

Wika: Amharic

Tagapakinig: General

Klase: Bible Stories & Teac

Layunin: Evangelism; Teaching

Kawikaan mula sa Bibliya: Paraphrase

Katayuan: Approved

Ang mga script ay panimulang gabay para sa pagsasalin at pagre-record sa ibat-ibang wika.Ang mga ito ay ay dapat na angkupin kung kinakailangan para maunawaan at makabuluhan sa bawat kultura at wika. Ilang termino at konsepto na ginamit ay maaaring gamitin para maipaliwanag o maaari di na palitan o tanggalin ng ganap.

Salita ng Talata

ኢየሱስ የሰይጣንን ፈተና ካሸፈነ በኋላ፣ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ይኖርበት ወደ ነበረው ወደገሊላ አውራጃ ተመለሰ። ኢየሱስ ከቦታ ወደ ቦታ እየሄደ አስተማረ።ሁሉም ሰው ስለ እርሱ መልካም ይናገሩ ነበር።

ኢየሱስ በልጅነቱ ወደ ኖረበት ወደ ናዝሬትከተማ ተመለሰ። በሰንበት ወደ አምልኮ ቦታ ሄደ።ያነብ ዘንድ የነቢዩን የኢሳይያስን ጥቅልልጽሑፍ ሰጡት። ኢየሱስ ጥቅልል ጽሑፉን ከፍቶ በከፊል ለሕዝቡ አነበበላቸው።

ኢየሱስ፣ “ለድሆች የምሥራችን፣ ለተማረኩት ነጻትን፣ ለዕውሮች ማየትን፣ ለታሰሩትም መፈታትን እሰብክዘንድ እግዚአብሔር መንፈሱን ሰጥቶኛል።ይህች የተወደደችውየጌታ ዓመት ነች” ብሎ አነበበ።

ከዚያም ኢየሱስ ተቀመጠ። ሁላቸውም በቅርበት ተመለከቱት። ልክ አሁን ያነበበው የእግዚአብሔር ቃል ምንባብ መሲሑን ያመለክት ነበር። ኢየሱስ፣“ይህ ያነበብኩላችሁ ቃል ልክአሁን እየተፈጸመ ነው” አለ።ሕዝቡ ሁሉ ተደነቁ። “ይህ የዮሴፍ ልጅ አይደለምን?” አሉ።

ከዚያም ኢየሱስ፣“ነቢይ በገዛ አገሩ እንደማይከበር እውነትነው፣ በነቢዩ ኤልያስ ዘመን፣ በእስራኤል ብዙ መበለቶች ነበሩ።ነገር ግን ለሦስትዓመት ተኩል ዝናብ ባልዘነበ ጊዜ እግዚአብሔር ኤልያስን በተለየአገር እንጂ በእስራኤልያለች መበለትን እንዲረዳ አልላከውም።”

ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መናገሩን ቀጠለ፣ “በነቢዩ ኤልሳዕ ዘመንም በእስራኤል የቆዳ ሕመም የያዛቸው ብዙ ሰዎች ነበሩ። ነገር ግን ኤልሳዕ አንዳቸውንም አልፈወሰም። የእስራኤል ጠላቶች አዛዥ የነበረውን የንዕማንን ቆዳ በሽታ ብቻ ፈወሰ።” ኢየሱስን ይሰሙ የነበሩት ሕዝብ አይሁዳውያን ነበሩ። ስለዚህ ይህን ሲናገር በሰሙት ጊዜ ተናደዱበት።

የናዝሬት ሕዝብ ኢየሱስን ከአምልኮው ቦታ ጐተቱትና ወርውረው ሊገድሉት ወደ ተራራውአፋፍ ወሰዱት።ነገር ግን ኢየሱስ በሕዝቡ መካከል ተራመደና ወደ ናዝሬትከተማ ሄደ።

ከዚያም ኢየሱስ በገሊላ አውራጃ ሁሉ ተዘዋወረ፣ ብዙ ሕዝብም ወደ እርሱ መጡ። ማየት፣ መራመድ፣ መስማት፣ ወይም መናገር የማይችሉትን ጨምሮ ብዙ የታመሙ ወይም የአካል ጕዳተኞች የሆኑ ሰዎችን አመጡ።

አጋንንት የነበሩባቸው ብዙ ሰዎችን ወደ ኢየሱስ አመጡ። በኢየሱስ ትእዛዝ አጋንንቱ ከሰዎቹ ወጡ፣ ብዙ ጊዜም፣ “አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ!” ብለው ጮኹ። ሕዝቡ ተደነቁና እግዚአብሔርን አመለኩ።

ከዚያም ኢየሱስደቀ መዛሙርቱ ተብለው የተጠሩትን ዐሥራ ሁለት ሰዎች መረጠ። ሐዋርያቱ ከኢየሱስ ጋር ተጓዙና ከእርሱ ተማሩ።

Katulad na kaalaman

Salita ng Buhay - Ang GRN ay mayroong mensahe sa audio sa libo-libong wika na naglalaman ng mensahe base sa Bibliya tungkul sa kaligtasan at Kristyanong pamumuhay.

Libreng mga download - Dito ay matatagpuan ang lahat ng pangunahing scripts mensahe ng GRN sa ibat-ibang wika, at mga larawan at iba pang katulad na materyales, ay maaari ng i-download.

Ang GRN Aklatang Audio - Pag-eebanghelyo at panimulang kagamitan ng katuruang Bibliya na angkop sa mga pangangailangan at kultura ng mga tao sa isang iba't ibang estilo at mga format.

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?