unfoldingWord 41 - እግዚአብሔር ኢየሱስን ከሙታን አስነሣው

unfoldingWord 41 - እግዚአብሔር ኢየሱስን ከሙታን አስነሣው

เค้าโครง: Matthew 27:62-28:15; Mark 16:1-11; Luke 24:1-12; John 20:1-18

รหัสบทความ: 1241

ภาษา: Amharic

ผู้ฟัง: General

ประเภท: Bible Stories & Teac

เป้าหมายของสื่อบันทึกเสียง: Evangelism; Teaching

ข้ออ้างอิงจากพระคัมภีร์: Paraphrase

สถานะ: Approved

บทความเป็นแนวทางพื้นฐานสำหรับการแปลและบันทึกเสียงภาษาอื่นๆ ควรดัดแปลงตามความจำเป็นเพื่อให้เข้าใจและเหมาะสมกับวัฒนธรรมและภาษาแต่ละภาษา คำศัพท์และแนวคิดบางคำที่ใช้อาจต้องอธิบายเพิ่มเติม หรือแทนที่ หรือตัดออก

เนื้อหาบทความ

ወታደሮቹ ኢየሱስን ከሰቀሉት በኋላ፣ የማያምኑት የአይሁድ መሪዎች ጲላጦስን፣ “ያ ውሸታም፣ ኢየሱስ፣ ከሦስት ቀን በኋላ ከሙታን እነሣለሁ ብሎአል። ደቀ መዛሙርቱ ሥጋውን እንዳይሰርቁትና ከሙታን ተነሣ እንዳይሉ ለማረጋገጥ አንድ ሰው መቃብሩን መጠበቅ አለበት” አሉት።

ጲላጦስ፣ “አንዳንድ ወታደሮችን ውሰዱና መቃብሩን በተቻለ መጠን እንዲጠበቅ አድርጉ” አለ። ስለዚህ በመቃብሩ መግቢያ ባለው ድንጋይ ላይ ማኅተም አደረጉና ሥጋውን ማንም እንዳይሰርቀው ለማረጋገጥ በዚያ ወታደሮችን አቆሙ።

ኢየሱስ ከተሰቀለ በኋላ የነበረ ቀን ሰንበት ነበረ። አይሁድ በዚያ ቀን ወደ መቃብር እንዲሄዱ አይፈቀድላቸውም ነበር። ስለዚህ ከሰንበት ቀን በኋላ በማለዳ ብዙ ሴቶች ሥጋው ላይ ተጨማሪ ሽቱ ለማርከፍከፍ ወደ ኢየሱስ መቃብር ሊሄዱ ተዘጋጁ።

በድንገትም ታላቅ የምድር መንቀጥቀጥ ሆነ። እንደ መብረቅ የሚያበራ መልአክ ከሰማይ ታየ። የመቃብሩን መግቢያ ከድኖ የነበረውን ድንጋይ አንከባለለና ተቀመጠበት። መቃብሩን ይጠብቁ የነበሩት ወታደሮች ፈሩና እንደ ሞቱ ሰዎች ሆነው መሬት ላይ ወደቁ።

ሴቶቹ ወደ መቃብሩ በደረሱ ጊዜ መልአኩ፣ “አትፍሩ ኢየሱስ እዚህ የለም። ልክ እነሣለሁ ብሎ እንደ ተናገረው ከሙታን ተነሥቶአል! መቃብሩን ተመልከቱና እዩ” ብሎ ነገራቸው። ሴቶቹ ወደ መቃብሩ ውስጥ ተመለከቱና የኢየሱስን ሥጋ ያኖሩበትን ስፍራ ዐዩ። ሥጋው በዚያ አልነበረም!

ከዚያም መልአኩ ለሴቶቹ፣ “ሂዱና ‘ኢየሱስ ከሙታን ተነሥቶአል ቀድሞአችሁ ወደ ገሊላ ይሄዳል ብላችሁ ለደቀ መዛሙርቱ ንገሩአቸው’” ብሎ ነገራቸው።

ሴቶቹ በፍርሃትና በታላቅ ደስታ ተሞልተው ነበር። የምሥራቹን ለደቀ መዛሙርቱ ለመንገር እየሮጡ ሄዱ።

ሴቶቹ የምሥራቹን ለደቀ መዛሙርቱ ለመንገር በመሄድ ላይ እያሉ፣ ኢየሱስ ታያቸው፣ እነርሱም ሰገዱለት። ኢየሱስ፣ “አትፍሩ። ወደ ገሊላ እንዲሄዱ ለደቀ መዛሙርቴ ንገሩአቸው። በዚያ ያዩኛል” አላቸው።

ข้อมูลที่เกี่ยวข้อง

สื่อบันทึกเสียงรูปแบบmp3, ซีดี, เทปคาสเซ็ท - องค์กรจีอาร์เอ็น มีสื่อบันทึกเสียงต่างๆ หลายพันภาษา เนื้อหาสื่อบันทึกเสียงตรงกับความจริงในพระคัมภีร์ เป็นเรื่องราวเกี่ยวกับความรอดและชีวิตคริสเตียน

ดาวน์โหลดฟรี - ที่นี่ท่านสามารถค้นหาบทความต่างๆ ของจีอาร์เอ็นในภาษาต่างๆ พร้อมทั้งภาพประกอบ และสื่ออื่นๆ ที่สามารถดาวน์โหลดได้

ห้องสมุดสื่อบันทึกเสียงข่าวประเสริฐของจีอาร์เอ็น - เจ็ดสิบกว่าปีที่นักบันทึกเสียงขององค์กรจีอาร์เอ็นได้บันทึกเสียงภาษาของชนกลุ่มน้อยต่างๆ และได้ผลิตสื่อบันทึกเสียงข่าวประเสริฐมากมาย

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?