unfoldingWord 29 - የምሕረት የለሹ ባሪያ ታሪክ

unfoldingWord 29 - የምሕረት የለሹ ባሪያ ታሪክ

เค้าโครง: Matthew 18:21-35

รหัสบทความ: 1229

ภาษา: Amharic

ผู้ฟัง: General

ประเภท: Bible Stories & Teac

เป้าหมายของสื่อบันทึกเสียง: Evangelism; Teaching

ข้ออ้างอิงจากพระคัมภีร์: Paraphrase

สถานะ: Approved

บทความเป็นแนวทางพื้นฐานสำหรับการแปลและบันทึกเสียงภาษาอื่นๆ ควรดัดแปลงตามความจำเป็นเพื่อให้เข้าใจและเหมาะสมกับวัฒนธรรมและภาษาแต่ละภาษา คำศัพท์และแนวคิดบางคำที่ใช้อาจต้องอธิบายเพิ่มเติม หรือแทนที่ หรือตัดออก

เนื้อหาบทความ

አንድ ቀን ጴጥሮስ ኢየሱስን፣ “መምህር ሆይ፣ ወንድሜ ቢበድለኝ ስንት ጊዜ ይቅር ልበለው? እስከ ሰባት ጊዜ ነውን?” ብሎ ጠየቀው። ኢየሱስ፣ “ሰባት ጊዜ አይደለም፣ ሰባ ጊዜ ሰባት እንጂ” አለው። ኢየሱስ ይህን ሲል ሁልጊዜ ይቅር ማለት አለብን ማለቱ ነው። ከዚያም ኢየሱስ ይህን ታሪክ ተናገረ።

ኢየሱስ እንዲህ አለ፣ “የእግዚአብሔር መንግሥት ባሮቹን ሊቈጣጠር የፈለገን ንጉሥ ትመስላለች። ከባሮቹ አንዱ የ10,000 መክሊት የሚያክል ከፍተኛ ዕዳ ነበረበት።”

ባሪያው ዕዳን መክፈል ስላልቻለ፣ ንጉሡ፣ “ዕዳውን ይከፍል ዘንድ ይህን ሰውና ቤተ ሰቡን ሽጡአቸው” አለው።

“ባሪያው በንጉሡ ፊት በጉልበቱ ወደቀና፣ ‘እባክህን ታገሠኝ፣ ያለብኝን ዕዳ ሁሉ እከፍልሃለሁ’ አለው። ንጉሡ ለባሪያው አዘነለት፣ ዕዳውንም ሁሉ ሰረዘለትና እንዲሄድ ለቀቀው።”

“ነገር ግን ባሪያው ከንጉሡ ዘንድ በወጣ ጊዜ፣ የአራት ወር ደመወዝ የሚሆን ዕዳ ያለበትን ባልንጀሮቹ ከሆኑት ባሪያዎች አንዱን አገኘ። ባሪያው ባልንጀራው የሆነውን ባሪያ ያዘውና፣ ‘ዕዳህን ክፈለኝ!’” አለው።

“ባልንጀራው ባሪያ በጉልበቱ ወድቆ፣ ‘እባክህን ታገሠኝ፣ ያለብኝን ዕዳ ሁሉ እከፍልሃለሁ’ አለው። ነገር ግን በዚህ ፈንታ ያ ባሪያ ባልንጀራ ባሪያውን ዕዳውን እስኪከፍለው ድረስ በወኅኒ ጣለው።”

“ሌሎች ባሮችም የሆነውን ነገር ዐይተው እጅግ ተረበሹ። ወደ ንጉሡ ሄደውም የሆነውን ነገር ሁሉ ነገሩት።”

“ንጉሡ ባሪያውን ጠራና፣ ‘አንተ ክፉ ባሪያ! ስለ ለመንኸኝ ዕዳህን ተውሁልህ። አንተም ይህንኑ ማድረግ ይገባህ ነበር’ አለው። ንጉሡ በጣም ተቈጣና ዕዳውን ሁሉ እስኪከፍል ድረስ ክፉውን ባሪያ በወኅኒ ጣለው።”

ከዚያም ኢየሱስ እንዲህ አለ፣ “ከእናንተ እያንዳንዱ ወንድሙን ይቅር ካላለ፣ እንዲሁ ደግሞ የሰማይ አባቴ ያደርግባችኋል።”

ข้อมูลที่เกี่ยวข้อง

สื่อบันทึกเสียงรูปแบบmp3, ซีดี, เทปคาสเซ็ท - องค์กรจีอาร์เอ็น มีสื่อบันทึกเสียงต่างๆ หลายพันภาษา เนื้อหาสื่อบันทึกเสียงตรงกับความจริงในพระคัมภีร์ เป็นเรื่องราวเกี่ยวกับความรอดและชีวิตคริสเตียน

ดาวน์โหลดฟรี - ที่นี่ท่านสามารถค้นหาบทความต่างๆ ของจีอาร์เอ็นในภาษาต่างๆ พร้อมทั้งภาพประกอบ และสื่ออื่นๆ ที่สามารถดาวน์โหลดได้

ห้องสมุดสื่อบันทึกเสียงข่าวประเสริฐของจีอาร์เอ็น - เจ็ดสิบกว่าปีที่นักบันทึกเสียงขององค์กรจีอาร์เอ็นได้บันทึกเสียงภาษาของชนกลุ่มน้อยต่างๆ และได้ผลิตสื่อบันทึกเสียงข่าวประเสริฐมากมาย

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?