unfoldingWord 39 - ኢየሱስ ለፍርድ ቀረበ
![unfoldingWord 39 - ኢየሱስ ለፍርድ ቀረበ](https://static.globalrecordings.net/300x200/z41_Mk_14_35.jpg)
Contur: Matthew 26:57-27:26; Mark 14:53-15:15; Luke 22:54-23:25; John 18:12-19:16
Numărul scriptului: 1239
Limba: Amharic
Public: General
Gen: Bible Stories & Teac
Scop: Evangelism; Teaching
Citat biblic: Paraphrase
Stare: Approved
Scripturile sunt linii directoare de bază pentru traducerea și înregistrarea în alte limbi. Acestea ar trebui adaptate după cum este necesar pentru a le face ușor de înțeles și relevante pentru fiecare cultură și limbă diferită. Unii termeni și concepte utilizate pot necesita mai multe explicații sau chiar pot fi înlocuite sau omise complet.
Textul scenariului
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z41_Mk_14_29.jpg)
አሁን ጊዜው እኩለ ሌሊት ነው። ሊቀ ካህናቱ ይጠይቀው ዘንድ ወታደሮቹ ኢየሱስን ወደ ሊቀ ካህናቱ ቤት ወሰዱት። ጴጥሮስ ራቅ ብሎ ከኋላ ተከተላቸው። ኢየሱስን ወደ ቤቱ ባስገቡት ጊዜ፣ ጴጥሮስ በውጪ ሆኖ እሳት ይሞቅ ነበር።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z41_Mk_14_31.jpg)
በቤቱ ውስጥ የአይሁድ መሪዎች ኢየሱስን ለፍርድ አቀረቡት። ስለ እርሱ የዋሹ ብዙ የሐሰት ምስክሮችን አመጡ። ይሁን እንጂ፣ ቃላቸው እርስ በርሱ አልተስማማም፣ ስለዚህ የአይሁድ መሪዎች ኢየሱስ በማንኛውም ነገር በደለኛ መሆኑን ማረጋገጥ አልቻሉም።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z41_Mk_14_33.jpg)
በመጨረሻ፣ ሊቀ ካህናቱ ኢየሱስን በቀጥታ ተመለከተውና፣ ንገረን፣ አንተ መሲሑ፣ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህን?" አለው።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z41_Mk_14_34.jpg)
ኢየሱስ፣ “እኔ ነኝ፣ እንዲሁም ከእግዚአብሔር ጋር ተቀምጬና ከሰማይ ስመጣ ታያለህ” አለው። ሊቀ ካህናቱ በቊጣ ልብሱን ቀደደና ወደ ሌሎቹ የሃይማኖት መሪዎች፣ “ተጨማሪ ምስክሮች አያስፈልጉም! የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ሲል ሰምታችሁታል። ፍርዳችሁ ምንድን ነው?” ብሎ ጮኸ።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z41_Mk_14_35.jpg)
ሁሉም የአይሁድ መሪዎች፣ “መሞት ይገባዋል!” ብለው ለሊቀ ካህናቱ መለሱለት። ከዚያም ኢየሱስን ፊቱን ሸፈኑት፣ ተፉበት፣ መቱት፣ ዘበቱበትም።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z41_Mk_14_36.jpg)
ጴጥሮስ ከቤቱ ውጪ በመጠባበቅ ላይ እያለ የቤት ሠራተኛ የሆነች ልጅ ዐየችውና፣ “አንተም ደግሞ ከኢየሱስ ጋር ነበርክ!” አለችው። ጴጥሮስ እርስዋ የተናገረችውን ካደ። ከዚያ በኋላ ሌላዋ የቤት ሠራተኛ ያንኑ ተናገረች፣ ጴጥሮስም እንደገና ካደ። በመጨረሻ ሕዝቡ “ሁለታችሁም ከገሊላ ስለሆናችሁ አንተ ከኢየሱስ ጋር መሆንህን እናውቃለን” አሉ።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z41_Mk_14_38.jpg)
ከዚያም ጴጥሮስ፣ “ይህንን ሰው የማውቀው ከሆነ የእግዚአብሔር መርገም በእኔ ላይ ይሁን! ብሎ ማለ። ወዲያውኑ ዶሮ ጮኸ፣ ኢየሱስም ዘወር አለና ጴጥሮስን ተመለከተው።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z41_Mk_14_39.jpg)
ጴጥሮስ ሄደና በምሬት አለቀሰ። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ኢየሱስን አሳልፎ የሰጠው ይሁዳ፣ የአይሁድ መሪዎች እንዲሞት በኢየሱስ ላይ እንደ ፈረዱበት ዐየ። ይሁዳ በሐዘን ተሞልቶ ሄደና ራሱን ገደለ።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z41_Mk_15_02.jpg)
በነጋታው ማለዳ ላይ የአይሁድ መሪዎች ኢየሱስን ወደ ሮማው ገዥ ወደ ጲላጦስ አመጡት። ጲላጦስ ኢየሱስን ጥፋተኛ ነህ ብሎ ይፈርድበትና በሞት እንዲቀጣ ያደርጋል ብለው ተስፋ አደረጉ። ጲላጦስ ኢየሱስን፣ “የአይሁድ ንጉሥ ነህን?” ብሎ ጠየቀው።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z41_Mk_15_03.jpg)
ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰለት፣ “አንተ አልህ፣ ነገር ግን መንግሥቴ ምድራዊ መንግሥት አይደለችም። እንደዚያ ብትሆን ኖሮ፣ አገልጋዮቼ ይዋጉልኝ ነበር። ስለ እግዚአብሔር እውነቱን ለመናገር ወደ ምድር መጥቼአለሁ። እውነትን የሚወድ ሁሉ እኔን ይሰማኛል።” ጲላጦስ፣ “እውነት ምንድን ነው?” አለ።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z41_Mk_15_04.jpg)
ጲላጦስ ከኢየሱስ ጋር ከተነጋገረ በኋላ ወደ ሕዝቡ ወጣና፣ “በዚህ ሰው ላይ ምንም በደል አላገኘሁበትም” አለ። የአይሁድ መሪዎችና ሕዝቡ ግን፣ “ስቀለው!” ብለው ጮኹ። ጲላጦስ፣ “በደለኛ አይደለም” ብሎ መለሰላቸው። እነርሱ ግን የበለጠ ጮኹ። ከዚያም ጲላጦስ ለሦስተኛ ጊዜ፣ “በደል የለበትም!” አለ።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z41_Mk_15_05.jpg)
ጲላጦስ ሕዝቡ መረበሽ ይጀምራሉ ብሎ ፈራ፣ ስለዚህ ኢየሱስን እንዲሰቅሉት ወታደሮቹን አዘዘ። የሮማ ወታደሮች ኢየሱስን ገረፉትና ቀይ ልብስ አለበሱት፣ እንዲሁም የሾኽ አክሊል በራሱ ላይ አደረጉ። ከዚያም፣ “እነሆ፣ የአይሁድ ንጉሥ!” በማለት ዘበቱበት።