unfoldingWord 25 - ሰይጣን ኢየሱስን ፈተነው

ਰੂਪਰੇਖਾ: Matthew 4:1-11; Mark 1:12-13; Luke 4:1-13

ਸਕ੍ਰਿਪਟ ਨੰਬਰ: 1225

ਭਾਸ਼ਾ: Amharic

ਦਰਸ਼ਕ: General

ਸ਼ੈਲੀ: Bible Stories & Teac

ਮਕਸਦ: Evangelism; Teaching

ਬਾਈਬਲ ਦੇ ਹਵਾਲੇ: Paraphrase

ਸਥਿਤੀ: Approved

ਲਿਪੀਆਂ ਦੂਜੀਆਂ ਭਾਸ਼ਾਵਾਂ ਵਿੱਚ ਅਨੁਵਾਦ ਅਤੇ ਰਿਕਾਰਡਿੰਗ ਲਈ ਬੁਨਿਆਦੀ ਦਿਸ਼ਾ-ਨਿਰਦੇਸ਼ ਹਨ। ਉਹਨਾਂ ਨੂੰ ਹਰੇਕ ਵੱਖਰੇ ਸੱਭਿਆਚਾਰ ਅਤੇ ਭਾਸ਼ਾ ਲਈ ਸਮਝਣਯੋਗ ਅਤੇ ਢੁਕਵਾਂ ਬਣਾਉਣ ਲਈ ਲੋੜ ਅਨੁਸਾਰ ਢਾਲਿਆ ਜਾਣਾ ਚਾਹੀਦਾ ਹੈ। ਵਰਤੇ ਗਏ ਕੁਝ ਨਿਯਮਾਂ ਅਤੇ ਸੰਕਲਪਾਂ ਲਈ ਵਧੇਰੇ ਵਿਆਖਿਆ ਦੀ ਲੋੜ ਹੋ ਸਕਦੀ ਹੈ ਜਾਂ ਪੂਰੀ ਤਰ੍ਹਾਂ ਬਦਲੀ ਜਾਂ ਛੱਡ ਦਿੱਤੀ ਜਾ ਸਕਦੀ ਹੈ।

ਸਕ੍ਰਿਪਟ ਟੈਕਸਟ

ኢየሱስ ከተጠመቀበኋላ ወዲያውኑ፣ መንፈስቅዱስ ወደምድረ በዳ ወሰደው፣ እዚያምአርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ። ከዚያም ሰይጣን ወደ ኢየሱስመጣና ኃጢአት እንዲሠራ ኢየሱስን ፈተነው።

“የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንክ፣ መብላት ትችል ዘንድ እነዚህን ድንጋዮች ወደእንጀራ ለውጥ” በማለት ሰይጣን ኢየሱስን ፈተነው።

ኢየሱስ፣ “‘ሰዎች ለመኖር እንጀራ ብቻ አያስፈልጋቸውም፣ነገር ግን እግዚአብሔር የሚናገረው እያንዳንዱ ቃል ያስፈልጋቸዋል’ተብሎ በእግዚአብሔር ቃል ተጽፎአል!” ብሎ መለሰለት።

ከዚያም ሰይጣን ኢየሱስን ወደ ቤተ መቅደስ ጫፍ ወሰደውና፣ “የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ ራስህን ወደ ታች ወርውር፣ ምክንያቱም፣ ‘ድንጋይ እግርህን እንዳይመታህ ይሸከሙህዘንድ እግዚአብሔር መላእክቱንያዛል ተብሎ ተጽፎል’” አለ።

ነገር ግን ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ቃል በመጥቀስ ለሰይጣን መለሰለት። “በእግዚአብሔር ቃል፣ ‘ጌታ አምላክህን አትፈታተነው’ በማለት ሕዝቡን ያዛል አለ።’”

ከዚያም ሰይጣን የዓለምን መንግሥታትና ክብራቸውን ሁሉ ዐሳየውና፣ “ወድቀህ ብትሰግድልኝይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ” አለ።

ኢየሱስ፣ “ሂድ፣ አንተ ሰይጣን! በእግዚአብሔር ቃልሕዝቡን፣ ‘ለጌታህ ለአምላክህ ስገድ እርሱንም ብቻአምልክ’ ብሎአዞአል” አለው።

ኢየሱስ ለሰይጣንፈተና አልተሸነፈም፣ ስለዚህ ሰይጣን ተወው። ከዚያ በኋላ መላእክት መጥተው ኢየሱስን አገለገሉት።

ਸੰਬੰਧਿਤ ਜਾਣਕਾਰੀ

Free downloads - Here you can find all the main GRN message scripts in several languages, plus pictures and other related materials, available for download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?