unfoldingWord 23 - የኢየሱስ ልደት

unfoldingWord 23 - የኢየሱስ ልደት

Samenvatting: Matthew 1-2; Luke 2

Scriptnummer: 1223

Taal: Amharic

Gehoor: General

Genre: Bible Stories & Teac

Doel: Evangelism; Teaching

Bijbelse verwijzing: Paraphrase

Toestand: Approved

De scripts dienen als basis voor de vertaling en het maken van opnames in een andere taal. Ze moeten aangepast worden aan de verschillende talen en culturen, om ze zo begrijpelijk en relevant mogelijk te maken. Sommige termen en begrippen moeten verder uitgelegd worden of zelfs weggelaten worden binnen bepaalde culturen.

Tekst van het script

ማርያም ዮሴፍ ለተባለ ጻድቅ ሰው ታጭታ ነበር። እጮኛዋ ዮሴፍ ማርያም መፀነስዋን በሰማ ጊዜ፣ ሕፃኑ የእርሱ እንዳልሆነ ዐወቀ። ማርያምን ለማሳፈር አልፈለገም፣ ስለዚህ ዝም ብሎ ሊፈታት ዐሰበ። ያንን ከማድረጉ በፊት መልአክ መጣና በሕልም ተናገረው።

መልአኩ እንዲህ አለ፡- “ዮሴፍ፣ ማርያምን ሚስት አድርገህ ለመውሰድ አትፍራ። በውስጥዋ ያለው ሕፃን ከመንፈስ ቅዱስ ነው። ወንድ ልጅ ትወልዳለች። ስሙን ኢየሱስ ብለህ ጥራው (ትርጕሙም፣ ‘ያሕዌ ያድናል’ ማለት ነው)፣ ምክንያቱም ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋል።”

ስለዚህ ዮሴፍ ማርያምን አገባትና ሚስቱ አድርጎ ወደ ቤቱ ወሰዳት፣ ነገር ግን እስክትወልድ ድረስ ከእርስዋ ጋር አልተኛም።

ማርያም የምትወልድበት ጊዜ እንደ ደረሰ፣ የሮማ መንግሥት ሁሉም ሰው ለቈጠራ ቅድማያቶቹ ወደ ኖሩበት ከተማ እንዲሄድ ተናገረ። ዮሴፍና ማርያም ከሚኖሩበት ከናዝሬት ወደ ቤተ ልሔም ረጅም ጕዞ ተጓዙ ምክንያቱም በቤተ ልሔም ከተማ የተወለደው ቅድማያታቸው ዳዊት ነበረ።

ወደ ቤተ ልሔም በደረሱ ጊዜ ማረፊያ ስፍራ አልነበረም። ሊያገኙ የቻሉት ብቸኛ ክፍል እንስሶች የሚያድሩበት ስፍራ ነበረ። ሕፃኑ በተወለደ ጊዜ የሚያስተኙበት አልጋ ስላልነበረ እናቱ በከብቶች መመገቢያ ገንዳ አስተኛችው። ስሙንም ኢየሱስ አሉት።

በዚያ ሌሊት በአቅራቢያው ባለ ሜዳ ላይ መንጎቻቸውን የሚጠብቁ ጥቂት እረኞች ነበሩ። በድንገት የሚያበራ መልአክ ታያቸው፣ እነርሱም ፈሩ። መልአኩ፣ “አትፍሩ፣ ምክንያቱም ለእናንተ የምሥራች አለኝ። መሲሑ፣ ጌታ በቤተልሔም ተወልዶአል!” አለ።

“ሄዳችሁ ሕፃኑን ፈልጉ፣ በጨርቅ ተጠቅልሎና በእንስሶች መመገቢያ ገንዳ ተኝቶ ታገኙታላችሁ።” ድንገትም ሰማያት በመላእክት ተሞሉ፣ እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ “ክብር ለእግዚአብሔር በሰማይ ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ!” አሉ።

እረኞች ኢየሱስ ወደ ነበረበት ስፍራ ፈጥነው ደረሱና ልክ መልአኩ እንደ ነገራቸው በእንስሶች መመገቢያ ገንዳ ተኝቶ አገኙት። በጣም ደስ አላቸው። ማርያምም ደግሞ በጣም ደስ አላት። እረኞቹ ስለ ሰሙትና ስላዩት ሁሉ እግዚአብሔርን እያመሰገኑ፣ በጎቻቸው ወደ ነበሩባቸው ሜዳዎች ተመለሱ።

ከጥቂት ጊዜ በኋላ ከሩቅ ምሥራቅ አገሮች የሆኑ ጠቢባን በሰማይ አንድ ያልተለመደ ኮከብ ዐዩ። ዐዲስ የአይሁድ ንጉሥ የተወለደ መሆኑን እንደሚያመለክት ተገነዘቡ። ስለዚህ ይህንን ንጉሥ ለማየት በጣም ረጅም ርቀት ተጓዙ። ወደ ቤተ ልሔም መጡና ኢየሱስና ወላጆቹ የነበሩበትን ቤት አገኙት።

ጠቢባኑ ኢየሱስን ከእናቱ ጋር ባዩት ጊዜ ወድቀው ሰገዱለት። ለኢየሱስ ውድ ስጦታዎች ሰጡት። ከዚያም ወደ አገራቸው ተመለሱ።

Verwante informatie

Woorden van Leven - GRN beschikt over audio opnamen in duizenden talen. Deze opnamen gaan over het verlossingsplan en het leven als christen.

Vrij te downloaden - Download Bijbelverhalen in audio formaat en Bijbellessen in duizenden talen, afbeeldingen, scripts en andere verwante materialen die geschikt zijn voor evangelisatie en gemeenteopbouw.

De GRN-audiobibliotheek - Evangelisatiemateriaal en basisbijbelonderricht, aangepast aan de behoeften en de cultuur van het volk, in verschillende stijlen en formaten.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons