unfoldingWord 14 - በምድረ በዳ ተቅበዘበዙ

unfoldingWord 14 - በምድረ በዳ ተቅበዘበዙ

Samenvatting: Exodus 16-17; Numbers 10-14; 20; 27; Deuteronomy 34

Scriptnummer: 1214

Taal: Amharic

Gehoor: General

Genre: Bible Stories & Teac

Doel: Evangelism; Teaching

Bijbelse verwijzing: Paraphrase

Toestand: Approved

De scripts dienen als basis voor de vertaling en het maken van opnames in een andere taal. Ze moeten aangepast worden aan de verschillende talen en culturen, om ze zo begrijpelijk en relevant mogelijk te maken. Sommige termen en begrippen moeten verder uitgelegd worden of zelfs weggelaten worden binnen bepaalde culturen.

Tekst van het script

እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር ያደረገው ቃል ኪዳን ክፍል ለሆኑት ሕግጋት እንዲታዘዙ ለእስራኤላውያን ከነገራቸው በኋላ፣ ከሲና ተራራ ሄዱ። እግዚአብሔር ሕዝቡን ከሲና ተራራ ከነዓን ተብላ ትጠራ ወደ ነበረችው ወደ ተስፋዪቱ ምድር ይመራቸው ጀመር። የደመናው ዓምድ ከፊት ለፊታቸው ወደ ከነዓን ሄደ፣ እነርሱም ተከተሉት።

እግዚአብሔር የተስፋዪቱን ምድር ለዘሮቻቸው እንደሚሰጣቸው ለአብርሃም፣ ለይስሐቅና ለያዕቆብ ተስፋ ሰጥቶአቸው ነበር፣ ነገር ግን አሁን በዚያች ምድር ብዙ የሕዝብ ወገኖች ይኖሩ ነበር። እነርሱም ከነዓናውያን ተብለው ይጠሩ ነበር። ከነዓናውያን እግዚአብሔርን አላመለኩትም ወይም አልታዘዙትም። ሐሰተኞች አማልክትን አመለኩ ብዙ ነገሮችንም አደረጉ።

እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን እንዲህ ብሎ ነገራቸው፣ “በተስፋዪቱ ምድር ያሉትን ከነዓናውያንን ሁሉ አጥፉአቸው። ከእነርሱ ጋር ሰላምን አታድርጉ አታግቡአቸውም። ጣዖቶቻቸውን ሁሉ ፈጽማችሁ አጥፉአቸው። ለእኔ ባትታዘዙ፣ በእኔ ፈንታ የእነርሱን ጣዖታት ታመልካላችሁ።”

እስራኤላውያን ወደ ከነዓን ድንበር በደረሱ ጊዜ፣ ሙሴ ከእያንዳንዱ የእስራኤል ነገድ አንድ አንድ ሰው፣ ዐሥራ ሁለት ሰዎችን መረጠ። ሄደው ምድሪቱ ምን እንደምትመስል እንዲሰልሉ መመሪያ ሰጣቸው። እነዚህ ሰዎች፣ ብርቱዎች ወይም ደካሞች መሆናቸውን ለማየት ከነዓናውያንን ደግሞ መሰለል ነበረባቸው።

ዐሥራ ሁለቱ ሰዎች በከነዓን ለአርባ ቀን ተጓዙና ተመልሰው መጡ። “ምድሪቱ በጣም ለም ነች ሰብሉም የተትረፈረፈ ነው!” ብለው ለሕዝቡ ነገሩአቸው። ዐሥሩ ሰላዮች ግን፣ “ከተሞቹ በጣም ብርቱዎች ሰዎቹም የገዘፉ ናቸው! ብንወጋቸው በእርግጥ ያሸንፉናል ይገድሉናልም!” አሉ።

ወዲያውኑ ሌሎቹ ሁለት ሰላዮች፣ ካሌብና ኢያሱ፣ “የከነዓን ሰዎች ረጃጅሞችና ብርቱዎች መሆናቸው እውነት ነው፣ ነገር ግን እኛ በእርግጥ እናሸንፋቸዋለን! እግዚአብሔር ስለ እኛ ይዋጋል!” አሉ።

ሕዝቡ ግን ካሌብንና ኢያሱን አልሰሙአቸውም። ሙሴንና አሮንን ተቈጡአቸውና፣ “ወደዚህ አስከፊ ቦታ ለምን አመጣችሁን? በጦርነት ከምንሞትና ሚስቶቻችን እንዲሁም ልጆቻችን ባሮች ከሚሆኑ ይልቅ በግብፅ ብንኖር ይሻለን ነበር” አሉ። ሕዝቡ ወደ ግብፅ መልሶ የሚወስዳቸው የተለየ መሪ ለመምረጥ ፈለጉ።

እግዚአብሔር በጣም ተቈጣና ወደ መገናኛው ድንኳ መጣ። እንዲህም አለ፣ “እናንተ በእኔ ላይ ስላመፃችሁ፣ ሕዝቡ ሁሉ በምድረ በዳ ይቅበዘበዛሉ። ከኢያሱና ከካሌብ በቀር ሃያ ዓመትና ከዚያ በላይ የሆናቸው ሁሉ በዚያ ይሞታሉ እንጂ ከቶ ወደ ተስፋዪቱ ምድር አይገቡም።”

ሕዝቡ ይህን በሰሙ ጊዜ፣ ኃጢአት በመሥራታቸው ዐዘኑ። የጦር መሣሪያዎቻቸውን ይዘው የከነዓንን ሰዎች ለመውጋት ሄዱ። ሙሴ እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር ስላልነበረ እንዳይሄዱ አስጠነቀቃቸው፣ ነገር ግን እርሱን አልሰሙትም።

እግዚአብሔር አብሮአቸው ወደ ጦርነቱ አልሄደም፣ ስለዚህ ተሸነፉ ብዙዎቻቸውም ተገደሉ። ከዚያም እስራኤላውያን ከከነዓን ተመለሱና በምድረ በዳ ለአርባ ዓመት ተቅበዘበዙ።

የእስራኤል ሕዝብ በምድረ በዳ በተቅበዘበዙባቸው አርባ ዓመታት እግዚአብሔር መገባቸው። ከሰማይ “መና” ተብሎ የሚጠራ እንጀራ ሰጣቸው። ደግሞም ሥጋ ይበሉ ዘንድ ወደ ሰፈራቸው ድርጭቶች ላከላቸው። በዚያን ጊዜ ሁሉ እግዚአብሔር ልብሳቸውና ጫማቸው እንዳያልቅ አደረገ።

እግዚአብሔር ተአምራዊ በሆነ መንገድ ውሃ እንኳ ከአለት ሰጣቸው። ይህም ሁሉ ሆኖ ግን የእስራኤል ሕዝብ በእግዚአብሔርና በሙሴ ላይ አማረሩ አጕረመረሙም። ቢሆንም፣ እግዚአብሔር ለአብርሃም፣ ለይስሐቅና ለያዕቆብ ለሰጠው ተስፋ አሁንም የታመነ ነበር።

ሕዝቡ ምንም ውሃ ባልነበራቸው በሌላ ጊዜ፣ እግዚአብሔር ለሙሴ፣ “አለቱን ተናገረው፣ ከእርሱም ውሃ ይወጣል” አለው። ነገር ግን ሙሴ ለአለቱ በመናገር ፈንታ በበትር ሁለት ጊዜ ስለመታው በሕዝቡ ሁሉ ፊት እግዚአብሔርን አዋረደ። ሁለም ሰው እንዲጠጣ ከአለቱ ውሃ ወጣ፣ ነገር ግን እግዚአብሔር በሙሴ ላይ ተቈጣና፣ “ወደ ተስፋዪቱ ምድር አትገባም” አለው።

እስራኤላውያን ለአርባ ዓመት በምድረ በዳ ከተቅበዘበዙ በኋላ፣ በእግዚአብሔር ላይ ያመፁት ሁሉ ሞቱ። ከዚያም እግዚአብሔር ሕዝቡን እንደ ገና ወደ ተስፋዪቱ ምድር ዳርቻ መራቸው። አሁን ሙሴ አርጅቶ ነበር፣ ስለዚህ ሕዝቡን በመምራት እንዲያግዘው እግዚአብሔር ኢየሱን መረጠ። ደግሞም እግዚአብሔር አንድ ቀን እንደ ሙሴ ያለ ሌላ ነቢይ እንደሚልክ ለሙሴ ተስፋ ሰጠው።

ከዚያም እግዚአብሔር የተስፋዪቱን ምድር ለማየት ይችል ዘንድ ወደ ተራራ ራስ ላይ እንዲወጣ ለሙሴ ነገረው። ሙሴ የተስፋዪቱን ምድር ዐየ፣ ነገር ግን እግዚአብሔር ወደ እርስዋ እንዲገባ አልፈቀደለትም። ከዚያም ሙሴ ሞተ፣ እስራኤላውያንም ለሠላሳ ቀናት ዐዘኑ። ኢያሱ ዐዲሱ መሪአቸው ሆነ። ኢያሱ በእግዚአብሔር ያመነና የታዘዘውም ስለ ነበር ጥሩ መሪ ነበር።

Verwante informatie

Woorden van Leven - GRN beschikt over audio opnamen in duizenden talen. Deze opnamen gaan over het verlossingsplan en het leven als christen.

Vrij te downloaden - Download Bijbelverhalen in audio formaat en Bijbellessen in duizenden talen, afbeeldingen, scripts en andere verwante materialen die geschikt zijn voor evangelisatie en gemeenteopbouw.

De GRN-audiobibliotheek - Evangelisatiemateriaal en basisbijbelonderricht, aangepast aan de behoeften en de cultuur van het volk, in verschillende stijlen en formaten.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons