unfoldingWord 36 - የኢየሱስ መልክ ተለወጠ

unfoldingWord 36 - የኢየሱስ መልክ ተለወጠ

Garis besar: Matthew 17:1-9; Mark 9:2-8; Luke 9:28-36

Nombor Skrip: 1236

Bahasa: Amharic

Penonton: General

Genre: Bible Stories & Teac

Tujuan: Evangelism; Teaching

Petikan Alkitab: Paraphrase

Status: Approved

Skrip ialah garis panduan asas untuk terjemahan dan rakaman ke dalam bahasa lain. Mereka harus disesuaikan mengikut keperluan untuk menjadikannya mudah difahami dan relevan untuk setiap budaya dan bahasa yang berbeza. Sesetengah istilah dan konsep yang digunakan mungkin memerlukan penjelasan lanjut atau bahkan diganti atau ditinggalkan sepenuhnya.

Teks Skrip

አንድ ቀን ኢየሱስ ሦስቱን ደቀ መዛሙርቱን ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ያዞ ሊጸልዩ ወደ ረጅም ተራራ ወጡ። ( ዮሐንስ የተባለው ደቀ መዝሙር ኢየሱስን ያጠመቀው ሰው አልነበረም።)

ኢየሱስ በመጸለይ ላይ እያለ፣ ፊቱ እንደ ፀሐይ አበራ፣ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ፣ በምድር ላይ ያለ ማንኛውም ሰው ሊያነጻው እስከማይችል ድረስ በጣም ነጭ ሆነ።

በዚያን ጊዜ ሙሴና ነቢዩ ኤልያስ ታዩ። እነዚህ ሰዎች በመቶዎች ከሚቈጠሩ ዓመታት በፊት በምድር ላይ ይኖሩ ነበር። በቅርቡ በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው ሞቱ ከኢየሱስ ጋር ተነጋገሩ።

ሙሴና ኤልያስ ከኢየሱስ ጋር በመነጋገር ላይ እያሉ ጴጥሮስ ኢየሱስን፣ “በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው። አንድ ለአንተ፣ አንድ ለሙሴ፣ እንዲሁም አንድ ለኤልያስ፣ ሦስት መጠለያዎችን እንሥራ” አለው። ጴጥሮስ የሚናገረውን አያውቅም ነበር።

ጴጥሮስ እየተናገረ እያለ፣ ብሩህ ደመና መጥቶ ከበባቸውና ከደመናው ድምፅ፣ “በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፣ እርሱን ስሙት” አለ። ሦስቱ ደቀ መዛሙርት ፈሩና መሬት ላይ ወደቁ።

ያኔ ኢየሱስ ዳሰሳቸውና፣ “አትፍሩ፣ ተነሡ” አላቸው። ዙሪያቸውን ሲያዩ ከኢየሱስ በቀር ማንም አልነበረም።

ኢየሱስና ሦስቱ ደቀ መዛሙርት ከተራራው ወረዱ። በዚያን ጊዜ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፣ “በዚህ ስለ ሆነው ነገር ገና ለማንም አትናገሩ። እኔ በቶሎ እሞታለሁ፣ ሕያውም እሆናለሁ። ከዚያ በኋላ ለሰዎች መናገር ትችላላችሁ።”

Maklumat berkaitan

Free downloads - Here you can find all the main GRN message scripts in several languages, plus pictures and other related materials, available for download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons