unfoldingWord 25 - ሰይጣን ኢየሱስን ፈተነው
![unfoldingWord 25 - ሰይጣን ኢየሱስን ፈተነው](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_04_04.jpg)
Тойм: Matthew 4:1-11; Mark 1:12-13; Luke 4:1-13
Скриптийн дугаар: 1225
Хэл: Amharic
Үзэгчид: General
Төрөл: Bible Stories & Teac
Зорилго: Evangelism; Teaching
Библийн ишлэл: Paraphrase
Статус: Approved
Скрипт нь бусад хэл рүү орчуулах, бичих үндсэн заавар юм. Тэдгээрийг өөр өөр соёл, хэл бүрт ойлгомжтой, хамааралтай болгохын тулд шаардлагатай бол тохируулсан байх ёстой. Ашигласан зарим нэр томьёо, ухагдахууныг илүү тайлбарлах шаардлагатай эсвэл бүр орлуулах эсвэл бүрмөсөн орхиж болно.
Скрипт Текст
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_04_01.jpg)
ኢየሱስ ከተጠመቀበኋላ ወዲያውኑ፣ መንፈስቅዱስ ወደምድረ በዳ ወሰደው፣ እዚያምአርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ። ከዚያም ሰይጣን ወደ ኢየሱስመጣና ኃጢአት እንዲሠራ ኢየሱስን ፈተነው።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_04_02.jpg)
“የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንክ፣ መብላት ትችል ዘንድ እነዚህን ድንጋዮች ወደእንጀራ ለውጥ” በማለት ሰይጣን ኢየሱስን ፈተነው።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_04_03.jpg)
ኢየሱስ፣ “‘ሰዎች ለመኖር እንጀራ ብቻ አያስፈልጋቸውም፣ነገር ግን እግዚአብሔር የሚናገረው እያንዳንዱ ቃል ያስፈልጋቸዋል’ተብሎ በእግዚአብሔር ቃል ተጽፎአል!” ብሎ መለሰለት።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_04_04.jpg)
ከዚያም ሰይጣን ኢየሱስን ወደ ቤተ መቅደስ ጫፍ ወሰደውና፣ “የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ ራስህን ወደ ታች ወርውር፣ ምክንያቱም፣ ‘ድንጋይ እግርህን እንዳይመታህ ይሸከሙህዘንድ እግዚአብሔር መላእክቱንያዛል ተብሎ ተጽፎል’” አለ።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_04_05.jpg)
ነገር ግን ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ቃል በመጥቀስ ለሰይጣን መለሰለት። “በእግዚአብሔር ቃል፣ ‘ጌታ አምላክህን አትፈታተነው’ በማለት ሕዝቡን ያዛል አለ።’”
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_04_06.jpg)
ከዚያም ሰይጣን የዓለምን መንግሥታትና ክብራቸውን ሁሉ ዐሳየውና፣ “ወድቀህ ብትሰግድልኝይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ” አለ።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_04_07.jpg)
ኢየሱስ፣ “ሂድ፣ አንተ ሰይጣን! በእግዚአብሔር ቃልሕዝቡን፣ ‘ለጌታህ ለአምላክህ ስገድ እርሱንም ብቻአምልክ’ ብሎአዞአል” አለው።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_04_08.jpg)
ኢየሱስ ለሰይጣንፈተና አልተሸነፈም፣ ስለዚህ ሰይጣን ተወው። ከዚያ በኋላ መላእክት መጥተው ኢየሱስን አገለገሉት።