unfoldingWord 25 - ሰይጣን ኢየሱስን ፈተነው

രൂപരേഖ: Matthew 4:1-11; Mark 1:12-13; Luke 4:1-13
മൂലരേഖ (സ്ക്രിപ്റ്റ്) നമ്പർ: 1225
ഭാഷ: Amharic
പ്രേക്ഷകർ: General
ഉദ്ദേശം: Evangelism; Teaching
Features: Bible Stories; Paraphrase Scripture
അവസ്ഥ: Approved
മറ്റ് ഭാഷകളിലേക്ക് വിവർത്തനം ചെയ്യുന്നതിനും റെക്കോർഡുചെയ്യുന്നതിനുമുള്ള അടിസ്ഥാന മാർഗ്ഗനിർദ്ദേശങ്ങളാണ് സ്ക്രിപ്റ്റുകൾ. ഓരോ വ്യത്യസ്ത സംസ്കാരത്തിനും ഭാഷയ്ക്കും അവ മനസ്സിലാക്കാവുന്നതും പ്രസക്തവുമാക്കുന്നതിന് അവ ആവശ്യാനുസരണം പൊരുത്തപ്പെടുത്തണം. ഉപയോഗിച്ച ചില നിബന്ധനകൾക്കും ആശയങ്ങൾക്കും കൂടുതൽ വിശദീകരണം ആവശ്യമായി വന്നേക്കാം അല്ലെങ്കിൽ രൂപാന്തരപ്പെടുത്തുകയോ പൂർണ്ണമായും ഒഴിവാക്കുകയോ ചെയ്യാം.
മൂലരേഖ (സ്ക്രിപ്റ്റ്) ടെക്സ്റ്റ്

ኢየሱስ ከተጠመቀበኋላ ወዲያውኑ፣ መንፈስቅዱስ ወደምድረ በዳ ወሰደው፣ እዚያምአርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ። ከዚያም ሰይጣን ወደ ኢየሱስመጣና ኃጢአት እንዲሠራ ኢየሱስን ፈተነው።

“የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንክ፣ መብላት ትችል ዘንድ እነዚህን ድንጋዮች ወደእንጀራ ለውጥ” በማለት ሰይጣን ኢየሱስን ፈተነው።

ኢየሱስ፣ “‘ሰዎች ለመኖር እንጀራ ብቻ አያስፈልጋቸውም፣ነገር ግን እግዚአብሔር የሚናገረው እያንዳንዱ ቃል ያስፈልጋቸዋል’ተብሎ በእግዚአብሔር ቃል ተጽፎአል!” ብሎ መለሰለት።

ከዚያም ሰይጣን ኢየሱስን ወደ ቤተ መቅደስ ጫፍ ወሰደውና፣ “የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ ራስህን ወደ ታች ወርውር፣ ምክንያቱም፣ ‘ድንጋይ እግርህን እንዳይመታህ ይሸከሙህዘንድ እግዚአብሔር መላእክቱንያዛል ተብሎ ተጽፎል’” አለ።

ነገር ግን ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ቃል በመጥቀስ ለሰይጣን መለሰለት። “በእግዚአብሔር ቃል፣ ‘ጌታ አምላክህን አትፈታተነው’ በማለት ሕዝቡን ያዛል አለ።’”

ከዚያም ሰይጣን የዓለምን መንግሥታትና ክብራቸውን ሁሉ ዐሳየውና፣ “ወድቀህ ብትሰግድልኝይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ” አለ።

ኢየሱስ፣ “ሂድ፣ አንተ ሰይጣን! በእግዚአብሔር ቃልሕዝቡን፣ ‘ለጌታህ ለአምላክህ ስገድ እርሱንም ብቻአምልክ’ ብሎአዞአል” አለው።

ኢየሱስ ለሰይጣንፈተና አልተሸነፈም፣ ስለዚህ ሰይጣን ተወው። ከዚያ በኋላ መላእክት መጥተው ኢየሱስን አገለገሉት።