unfoldingWord 27 - የደጉ ሳምራዊ ታሪክ

unfoldingWord 27 - የደጉ ሳምራዊ ታሪክ

Kontūras: Luke 10:25-37

Scenarijaus numeris: 1227

Kalba: Amharic

Publika: General

Žanras: Bible Stories & Teac

Tikslas: Evangelism; Teaching

Biblijos citata: Paraphrase

Būsena: Approved

Scenarijai yra pagrindinės vertimo ir įrašymo į kitas kalbas gairės. Prireikus jie turėtų būti pritaikyti, kad būtų suprantami ir tinkami kiekvienai kultūrai ir kalbai. Kai kuriuos vartojamus terminus ir sąvokas gali prireikti daugiau paaiškinti arba jie gali būti pakeisti arba visiškai praleisti.

Scenarijaus tekstas

አንድ ቀን አንድ የአይሁድ ሕግ ዐዋቂ ሊፈትነው ወደ ኢየሱስ መጣ፣ “መምህር ሆይ፣ የዘላለምን ሕይወት እንድወርስ ምን ላድርግ?” አለው። ኢየሱስ፣ “በእግዚአብሔር ሕግ የተጻፈው ምንድን ነው?” ብሎ መለሰለት።

ሕግ ዐዋቂው የእግዚአብሔርሕግ፣ “ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም ኃይልህም በፍጹም ዐሳብህም ውደድ። ባልንጀራህንም እንደ ራስህ ውደድ” ይላል ብሎ መለሰ። ኢየሱስ፣ “ትክክል ነህ! ይህን አድርግ በሕይወትም ትኖራለህ” አለው።

ነገር ግን ሕግ ዐዋቂው ጻድቅ መሆኑን ለማረጋገጥ ፈለገ፣ ስለዚህ፣ “ባልንጀራዬ ማን ነው?” ብሎ ጠየቀ።

ኢየሱስ ታሪክ በመናገር ለሕግ ዐዋቂው መለሰለት። “ከኢየሩሳሌም ወደ ኢያሪኮ ይጓዝ የነበረ አንድ አይሁዳዊ ነበረ።”

“ሰውዬው በመጓዝ ላይ እያለ ወንበዴዎች ያዙት። የነበረውን ነገር ሁሉ ወሰዱበትና እስኪሞት ድረስ ደበደቡት። ከዚያም ሄዱ።”

ከዚያ በኋላ ወዲያውኑ አንድ አይሁዳዊ ካህን በዚያ መንገድ ይጓዝ ነበር። ይህ የሃይማኖት መሪ የተዘረፈውንና የተደበደበውን ሰው ባየ ጊዜ ወደ መንገዱ ሌላኛ ጎን ሄደ፣ ርዳታ የፈለገውን ሰው ቸል አለውና ጕዞውን ቀጠለ።"

ከዚያ በኋላ ብዙም ሳይቆይ፣አንድ ሌዋዊ መጣ።( ሌዋውያን በቤተ መቅደስ ካህናቱን የሚረዱ የአይሁድ ነገድ ነበሩ።) ሌዋዊውም ደግሞ ወደ መንገዱ ሌላኛ ጎን ተሻገረና የተዘረፈውንና የተደበደበውን ሰው በቸልታ አለፈው።"

በዚያ መንገድ የወረደው የሚቀጥለው ሰው ሳምራዊ ነበር።(ሳምራውያን የሌሎች አገሮች ሰዎችን ያገቡ የአይሁድ ዝርያዎች ነበሩ።ሳምራውያንና አይሁዳውያን እርስ በርስ ይጠላሉ ነበር።) ነገር ግን ሳምራዊው አይሁዳዊውን ባየ ጊዜ በጣም አድርጎ ራራለት። ስለዚህ ተንከባከበውና ቊስሉን አሰረለት።"

“ከዚያ በኋላ ሳምራዊው ሰውዬውን አንሥቶ በራሱ አህያ ላይ አስቀምጦት ወደ እንግዶች ማደሪያ ወሰደው ተንከባከበውም።”

“በማግሥቱም ሳምራዊው ጕዞውን መቀጠል አስፈለገው። ለእንግዶች ማረፊያው ባለቤት ጥቂት ገንዘብ ሰጠውና፣”ተንከባከበው፣ ከዚህ ሌላ ገንዘብ የምታወጣ ከሆነ በምመለስበት ጊዜ እከፍልሃለሁ አለው።"

ከዚያ በኋላ ኢየሱስ ሕግ ዐዋቂውን፣ “ምን ታስባለህ? ለተዘረፈውና ለተደበደበው ሰው ባልንጀራው ከሦስቱ ሰዎች የትኛው ነበር?” ብሎ ጠየቀው። እርሱም፣ “ምሕረት ያደረገለት ነበር” ብሎ መለሰለት። ኢየሱስ፣ “አንተም ሄደህ እንደዚሁ አድርግ” ብሎ ነገረው።

Susijusi informacija

Free downloads - Here you can find all the main GRN message scripts in several languages, plus pictures and other related materials, available for download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?