unfoldingWord 35 - የርኅሩኁ አባት ታሪክ

unfoldingWord 35 - የርኅሩኁ አባት ታሪክ

Контур: Luke 15

Скрипт номери: 1235

Тил: Amharic

Аудитория: General

Жанр: Bible Stories & Teac

Максат: Evangelism; Teaching

Библиядан цитата: Paraphrase

Статус: Approved

Скрипттер башка тилдерге которуу жана жазуу үчүн негизги көрсөтмөлөр болуп саналат. Ар бир маданият жана тил үчүн түшүнүктүү жана актуалдуу болушу үчүн алар зарыл болгон ылайыкташтырылышы керек. Колдонулган кээ бир терминдер жана түшүнүктөр көбүрөөк түшүндүрмөлөрдү талап кылышы мүмкүн, ал тургай алмаштырылышы же толук алынып салынышы мүмкүн.

Скрипт Текст

አንድ ቀን ኢየሱስ ብዙ ቀረጥ ሰብሳቢዎችንና ሊሰሙት የተሰበሰቡ ሌሎች ኃጢአተኞችን ያስተምር ነበር።

ደግሞም በዚያ የነበሩ አንዳንድ የሃይማኖት መሪዎች ኢየሱስ ኃጢአተኞችን ወዳጆች አድርጎ ሲቀበላቸው ዐዩ፣ እርስ በርሳቸውም ይነቅፉት ጀመር። ስለዚህ ኢየሱስ ይህንን ታሪክ ነገራቸው።

ሁለት ልጆች ያሉት አንድ ሰው ነበር። ታናሹ ልጅ አባቱን፣ አባቴ ሆይ፣ ከገንዘብህ የሚደርሰኝን ክፍል አሁን ስጠኝ!’ አለው። ስለዚህ አባትዬው ገንዘቡን ለሁለቱ ልጆቹ አካፈላቸው።"

“ታናሹ ልጅ ወዲያውኑ ያለውን ሁሉ ሰበሰበና ሩቅ አገር ሄዶ በኃጢአት እየኖረ ገንዘቡን አጠፋ።

“ከዚያ በኋላ ታናሹ ልጅ በነበረበት አገር ጽኑ ረሀብ ሆነ፣ ምግብ የሚገዛበት ገንዘብም አልነበረውም። ስለዚህ ብቸኛ የነበረውን፣ እሪያዎችን የመመገብ ሥራ ያዘ። በጣም ተጐሳቊሎና ተርቦ ስለ ነበር የእሪያዎችን ምግብ ለመብላት ይመኝ ነበር።”

“በመጨረሻ፣ ታናሹ ልጅ ለራሱ እንዲህ አለ፣ ‘ምን እያደረግሁ ነው? የአባቴ አገልጋዮች ሁሉ የሚበሉት ብዙ ምግብ አላቸው፣ እኔ ግን ተርቤአለሁ። ወደ አባቴ ተመልሾ እሄድና ከአገልጋዮቹ አንዱ እንዲያደርገኝ እለምነዋለሁ።’”

ስለዚህ ታናሹ ልጅ ወደ አባቱ ቤት መመለስ ጀመረ። ገና በሩቅ እያለ አባቱ ዐየውና አዘነለት። ወደ ልጁ ሮጠና አቀፈው ሳመውም።"

“ልጁም አለ፣ ‘አባቴ ሆይ፣ እግዚአብሔርንና አንተን በድዬአለሁ። ልጅህ ልባል አይገባም።’”

“ነገር ግን አባቱ ከአገልጋዮቹ ለአንዱ እንዲህ ብሎ ነገረው፣ ‘ፈጥነህ ሂድና ማለፊያ ልብስ አምጥተህ ለልጄ አልብሰው! ለጣቱ ቀለበት ለእግሩም ጫማ አድርግለት። ከዚያም እንበላና ደስ ይለን ዘንድ የሰባ ፍሪዳ አምጥታችሁ እረዱ፣ ምክንያቱም ይህ ልጄ ሞቶ ነበር፣ ሕያውም ሆኖአል! ጠፍቶ ነበር፣ አሁን ግን ተገኝቶአል!’”

“ስለዚህ ሰዎቹ ደስ ይላቸው ጀመር። ብዙ ሳይቆይ፣ ይሠራበት ከነበረው እርሻ ታላቅ ወንድሙ ወደ ቤት መጣ። የሙዚቃና የዘፈን ድምፅ ሰማ፣ ምን እየሆነ ነው ብሎም ተገረመ።”

“ታላቁ ልጅ ወንድሙ ስለ መጣ እየተደሰቱ መሆናቸውን ባወቀ ጊዜ፣ በጣም ስለ ተቈጣ ወደ ቤት ለመግባት ፈቃደኛ አልሆነም። አባቱ ወጣና ገብቶ ከእነርሱ ጋር እንዲደሰት ለመነው፣ እርሱ ግን እምቢ አለ።”

ታላቁ ልጅ አባቱን እንዲህ አለው፣ ‘በእነዚህ ዓመታት ሁሉ በታማኝነት ለአንተ ሠርቼአለሁ! ከቶ ትእዛዝህን አልተላለፍኩም፣ እስካሁንም ከጓደኞቼ ጋር እንድደሰት አንድ ጥቦት ፍየል እንኳ አልሰጠኸኝም። ኃጢአት በመሥራት ገንዘብህን ያጠፋው ይህ ልጅህ ግን ወደ ቤት በመጣ ጊዜ፣ የሰባ ፍሪዳ አረድህለት!"

“አባቱ እንዲህ ብሎ መለሰለት፣ ‘ልጄ፣ አንተ ሁልጊዜ ከእኔ ጋር ነህ፣ ያለኝም ነገር ሁሉ የአንተ ነው። መደሰታችን ግን ትክክል ነው፣ ምክንያቱም ወንድምህ ሞቶ ነበር፣ አሁን ግን ሕያው ሆኖአል። ጠፍቶ ነበር፣ አሁን ግን ተገኝቶአል!”

Байланыштуу маалымат

Free downloads - Here you can find all the main GRN message scripts in several languages, plus pictures and other related materials, available for download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?