unfoldingWord 36 - የኢየሱስ መልክ ተለወጠ
개요: Matthew 17:1-9; Mark 9:2-8; Luke 9:28-36
스크립트 번호: 1236
언어: Amharic
청중: General
장르: Bible Stories & Teac
목적: Evangelism; Teaching
성경 인용: Paraphrase
지위: Approved
이 스크립트는 다른 언어로 번역 및 녹음을위한 기본 지침입니다. 그것은 그것이 사용되는 각 영역에 맞게 다른 문화와 언어로 조정되어야 합니다. 사용되는 몇 가지 용어와 개념은 다른 문화에서는 다듬어지거나 생략해야 할 수도 있습니다.
스크립트 텍스트
አንድ ቀን ኢየሱስ ሦስቱን ደቀ መዛሙርቱን ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ያዞ ሊጸልዩ ወደ ረጅም ተራራ ወጡ። ( ዮሐንስ የተባለው ደቀ መዝሙር ኢየሱስን ያጠመቀው ሰው አልነበረም።)
ኢየሱስ በመጸለይ ላይ እያለ፣ ፊቱ እንደ ፀሐይ አበራ፣ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ፣ በምድር ላይ ያለ ማንኛውም ሰው ሊያነጻው እስከማይችል ድረስ በጣም ነጭ ሆነ።
በዚያን ጊዜ ሙሴና ነቢዩ ኤልያስ ታዩ። እነዚህ ሰዎች በመቶዎች ከሚቈጠሩ ዓመታት በፊት በምድር ላይ ይኖሩ ነበር። በቅርቡ በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው ሞቱ ከኢየሱስ ጋር ተነጋገሩ።
ሙሴና ኤልያስ ከኢየሱስ ጋር በመነጋገር ላይ እያሉ ጴጥሮስ ኢየሱስን፣ “በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው። አንድ ለአንተ፣ አንድ ለሙሴ፣ እንዲሁም አንድ ለኤልያስ፣ ሦስት መጠለያዎችን እንሥራ” አለው። ጴጥሮስ የሚናገረውን አያውቅም ነበር።
ጴጥሮስ እየተናገረ እያለ፣ ብሩህ ደመና መጥቶ ከበባቸውና ከደመናው ድምፅ፣ “በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፣ እርሱን ስሙት” አለ። ሦስቱ ደቀ መዛሙርት ፈሩና መሬት ላይ ወደቁ።
ያኔ ኢየሱስ ዳሰሳቸውና፣ “አትፍሩ፣ ተነሡ” አላቸው። ዙሪያቸውን ሲያዩ ከኢየሱስ በቀር ማንም አልነበረም።
ኢየሱስና ሦስቱ ደቀ መዛሙርት ከተራራው ወረዱ። በዚያን ጊዜ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፣ “በዚህ ስለ ሆነው ነገር ገና ለማንም አትናገሩ። እኔ በቶሎ እሞታለሁ፣ ሕያውም እሆናለሁ። ከዚያ በኋላ ለሰዎች መናገር ትችላላችሁ።”