unfoldingWord 22 - የዮሐንስ መወለድ
개요: Luke 1
스크립트 번호: 1222
언어: Amharic
청중: General
장르: Bible Stories & Teac
목적: Evangelism; Teaching
성경 인용: Paraphrase
지위: Approved
이 스크립트는 다른 언어로 번역 및 녹음을위한 기본 지침입니다. 그것은 그것이 사용되는 각 영역에 맞게 다른 문화와 언어로 조정되어야 합니다. 사용되는 몇 가지 용어와 개념은 다른 문화에서는 다듬어지거나 생략해야 할 수도 있습니다.
스크립트 텍스트
አስቀድሞ እግዚአብሔር በመላእክቱና በነቢያቱ በኩል ለሕዝቡ ተናግሮ ነበር። ነገር ግን ለእነርሱ ያልተናገረባቸው 400 ዓመታት አለፉ። በድንገት አንድ መልአክ ዘካርያስ ተብሎ ወደሚጠራ ሽማግሌ ካህን ከእግዚአብሔር ዘንድ መልእክት ይዞ መጣ። ዘካርያስና ሚስቱ ኤልሳቤጥ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች ነበሩ፣ ነገር ግን እርስዋ ልጆችን መውለድ አልቻለችም ነበር።
መልአኩ ዘካርያስን አለው፣ “ሚስትህ ወንድ ልጅ ትወልዳለች። ዮሐንስ ብለህ ተጠራዋለህ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ ይሞላል፣ ሕዝቡንም ለመሲሑ ያዘጋጃል!” ዘካርያስ፣ “ሚስቴና እኔ ልጆችን ለመውለድ በጣም አርጅተናል! ይህ እንደሚሆን እንዴት ዐውቃለሁ?” ብሎ መለሰ።
መልአኩ ለዘካርያስ እንዲህ ብሎ መለሰለት፣ ይህን የምሥራች እንዳመጣላችሁ እግዚአብሔር ላከኝ። ስላላመንከኝ፣ ልጁ እስኪወለድ ድረስ መናገር አትችልም።" ወዲያኑ ዘካርያስ መናገር አልቻለም። ከዚያ በኋላ መልአኩ ከዘካርያስ ተለየ። ዘካርያስም ወደ ቤት ተመለሰ ሚስቱም ፀነሰች።
ኤልሳቤጥ የስድስት ወር ነፍሰ ጡር በነበረች ጊዜ፣ ያው መልአክ በድንገት ስምዋ ማርያም ለተባለ ለኤልሳቤጥ ዘመድ ተገለጠ። እርስዋ ድንግል ነበረችና ልታገባ ዮሴፍ ለተባለ ሰው ታጭታ ነበር። መልአኩ፣ “ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ። ስሙን ኢየሱስ ትዪዋለሽ። እርሱም የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ይባላል ለዘላለምም ገዥ ይሆናል” አለ።
ማርያም “እኔ ድንግል ስለ ሆንኩ፣ ይህ እንዴት ይሆናል?” ብላ መለሰች። መልአኩ እንዲህ ብሎ አብራራ፣ “መንፈስ ቅዱስ ወደ አንቺ ይመጣል፣ የልዑል ኃይል ይጸልልሻል። ስለዚህ ልጁ ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይሆናል።” ማርያም አመነች መልአኩ ያለውንም ተቀበለች።
መልአኩ ለማርያም ከተናገረ በኋላ ወዲያወኑ፣ ሄደችና ኤልሳቤጥን ጐበኘቻት። ኤልሳቤጥ የማርያምን ሰላምታ እንደ ሰማች፣ የኤልሳቤጥ ልጅ በሆዷ ውስጥ ዘለለ። ሴቶቹ እግዚአብሔር ስላደረገላቸው ነገር አብረው ሐሤት አደረጉ። ማርያም ኤልሳቤጥን ለሦስት ወራት ከጐበኘቻት በኋላ፣ ማርያም ወደ ቤትዋ ተመለሰች።
ኤልሳቤጥ ወንድ ልጅዋን ከወለደች በኋላ፣ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ መልአኩ እንዳዘዘው ሕፃኑን ዮሐንስ ብለው ሰየሙት። በዚያን ጊዜ እግዚአብሔር ለዘካርያስ እንደ ገና እንዲናገር ፈቀደለት። ዘካርያስ እንዲህ አለ፣ “ሕዝቡን ዐስቦአልና እግዚአብሔር ይመስገን! አንተም ልጄ፣ ለኃጢአታቸው ይቅርታ መቀበል እንዴት እንደሚችሉ ለሕዝቡ የምትናገር የልዑል እግዚአብሔር ነቢይ ትባላለህ!”