unfoldingWord 07 - እግዚአብሔር ያዕቆብን ባረከ

개요: Genesis 25:27-35:29
스크립트 번호: 1207
언어: Amharic
청중: General
장르: Bible Stories & Teac
목적: Evangelism; Teaching
성경 인용: Paraphrase
지위: Approved
이 스크립트는 다른 언어로 번역 및 녹음을위한 기본 지침입니다. 그것은 그것이 사용되는 각 영역에 맞게 다른 문화와 언어로 조정되어야 합니다. 사용되는 몇 가지 용어와 개념은 다른 문화에서는 다듬어지거나 생략해야 할 수도 있습니다.
스크립트 텍스트

ልጆቹም እንዳደጉ ያዕቆብ ከእናቱ ጋር በቤት መቆየትን ይወድ ነበር። ኤሳው ግን አደን ማደን ይወድ ነበር። ርብቃ ያዕቆብን ትወድደው ነበር፣ ይስሐቅ ግን ኤሳውን ይወድደው ነበር።

ከዕለታት አንድ ቀን ኤሳው ከአደን ተመልሶ ሲመጣ በጣም ተርቦ ነበር። ኤሳው ያዕቆብን “እባክህ ካዘጋጀኸው ምግብ ትንሽ ስጠኝ” አለው። ያዕቆብም በመጀመሪያ የብኩርናህን መብት ስጠኝ ሲል መለሰለት። ስለዚህም ኤሳው የብኩርናውን መብት ለያዕቆብ ሰጠው ከዚያም ያዕቆብ ከሠራው ምግብ ሰጠው።

ይስሐቅ በረከቱን ለኤሳው ሊሰጠው ፈለገ።ነገር ግንይህን ከማድረጉበፊት ርብቃና ያዕቆብ ይስሐቅን አታለሉት። ያዕቆብ ኤሳውንመስሎ ወደ ይስሐቅ ቀረበ። ይስሐቅ አርጅቶነበር ማየትም አይችልም ነበር። ስለዚህም ያዕቆብ የኤሳውን ልብሶችለብሶ የፍየልለምድ በአንገቱናበእጁ አድርጎ ወደ ይስሐቅ በመቅረብ ይስሐቅን አታለለው።

ያዕቆብ ወደ ኤሳው መጣና እንዲህ አለው፣ “እኔ ኤሳው ነኝ መጥቻለሁና ልትባርከኝ ትችላለህ” ይስሐቅ የፍየሉን ፀጉር ዳሰሰና የልብሱንም ጠረን አሽትቶ ኤሳው እንደ ሆነ አሰበና ባረከው።

ያዕቆብ የብኵርና መብቱንና በረከቱን አታልሎ ስለ ወሰደበት ኤሳው ያዕቆብን ጠላው አባታቸው ከሞተ በኋላ ሊገድለውም አሰበ።

ነገር ግን ርብቃ የኤሳውን እቅድ ሰማች። ስለዚህም እሷና ይስሐቅ ከዘመዶቹ ጋር እንዲኖር ወደ ሩቅ አገር ያዕቆብን ሰደዱት።

ያዕቆብ ለረዥም ዓመታት ከርብቃ ዘመዶች ጋር ኖረ። በዚያም ጊዜ ትዳር መስርቶ 12 ወንዶች ልጆችና 1 ሴት ልጅ ወለደ። እግዚአብሔርም በጣም አበለጸገው።

በከነዓን ከኖረበት ከሃያ (20) ዓመታት በኋላ ያዕቆብ ከቤተ ሰቡ፣ ከሠራተኞቹና ከመንጋው ሁሉ ጋር ወደ ከነዓን ምድር ለመመለስ ወሰነ።

ኤሳው አሁንም ሊገድለኝ ያስብ ይሆናል ብሎ በልቡ ስላሰበ ያዕቆብ ፈራ። ስለዚህም የእጅ መንሻ እንዲሆነው የብዙ ከብቶች መንጋ ስጦታ አድርጎ ለኤሳው ላከለት። ከብቶቹን ያመጡለት የያዕቆብ አገልጋዮች ኤሳውን “አገልጋይህ ያዕቆብ እነዚህን ከብቶች ልኮልሃል እርሱም በቅርቡ ይመጣል” አሉት።

ኤሳው ግን ቀድሞውኑ ያዕቆብን ይቅር ብሎት ስለ ነበር ዳግም ለመገናኘት ደስተኞች ነበሩ። ያዕቆብ በከነዓን ምድር በሰላም ኖረ፤ ከዚያም ይስሐቅ ሞተ ያዕቆብና ኤሳው ቀበሩት እግዚአብሔር ለአብርሃም የገባለት የቃል ኪዳኑ ተስፋ አሁን ከይስሐቅ ወደ ያዕቆብ ተላለፈ።