unfoldingWord 11 - ፋሲካ
მონახაზი: Exodus 11:1-12:32
სკრიპტის ნომერი: 1211
Ენა: Amharic
აუდიტორია: General
ჟანრი: Bible Stories & Teac
მიზანი: Evangelism; Teaching
ბიბლიური ციტატა: Paraphrase
სტატუსი: Approved
სკრიპტები არის ძირითადი სახელმძღვანელო სხვა ენებზე თარგმნისა და ჩაწერისთვის. ისინი საჭიროებისამებრ უნდა იყოს ადაპტირებული, რათა გასაგები და შესაბამისი იყოს თითოეული განსხვავებული კულტურისა და ენისთვის. ზოგიერთ ტერმინს და ცნებას შეიძლება დასჭირდეს მეტი ახსნა ან ჩანაცვლება ან მთლიანად გამოტოვება.
სკრიპტის ტექსტი
እስራኤላውያንን ካልለቀቀ የሰዎችንና የእንስሳትን ተባዕት በኵር ሁሉ እንደሚገድል እግዚአብሔር ፈርዖንን አስጠነቀቀው። ፈርዖን ይህን በሰማ ጊዜ፣ አሁንም ማመንና ለእግዚአብሔር መታዘዝ እምቢ አለ።
እግዚአብሔር በእርሱ ያመነ የማንኛውም ሰው በኵር ወንድ ልጅ ለማዳን መንገድ አዘጋጀ። እያንዳንዱ ቤተ ሰብ ፍጹም የሆነ ጠቦት መርጦ አረደ።
እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን የጠቦቱን ደም በቤታቸው በር ላይ እንዲቀቡት፣ ሥጋውንም ጠብሰው ያለ እርሾ ከተጋገረው ቂጣ ጋር በፍጥነት እንዲበሉት ነገራቸው። ደግሞ በበሉት ጊዜ ከግብፅ ለመውጣት እንዲዘጋጁ ነገራቸው።
እስራኤላውያን ልክ እግዚአብሔር እንዲያደርጉ እንዳዘዛቸው ሁሉንም ነገር አደረጉ። እኩለ ሌሊት ላይ እግዚአብሔር በመላው ግብፅ አልፎ ወንድ በኵርን ሁሉ ገደለ።
የእስራኤላውያን ቤቶች ሁሉ በሮቻቸው ደም ተቀብተው ነበር፣ ስለዚህ እግዚአብሔር በቤቶቹ አለፈ። በቤቶቹ ውስጥ የነበረው ሰው ሁሉ ዳነ። እስራኤላውያን በጠቦቱ ደም ምክንያት ዳኑ።
ግብፃውያን ግን በእግዚአብሔር አላመኑም፣ ትእዛዛቱንም አልፈጸሙም። ስለዚህ እግዚአብሔር በቤቶቻቸው አላለፈም። እግዚአብሔር የግብፃውያንን በኵር ወንዶችን ሁሉ ገደለ።
በእስር ቤት ካለው በኵር እስረኛ ጀምሮ እስከ ፈርዖን በኵር ድረስ እያንዳንዱ ግብፃዊ በኵር ወንድ ሞተ። ከጥልቅ ሐዘናቸው የተነሣ በግብፅ የነበሩ ብዙ ሰዎች ያለቅሱና ይጮኹ ነበር።
በዚያው ሌሊት ፈርዖን ሙሴንና አሮንን ጠርቶ፣ “እስራኤላውያንን ይዛችሁ አሁኑኑ ሂዱ!” አላቸው።