unfoldingWord 30 - ኢየሱስ አምስት ሺህ ሰዎችን መገበ

unfoldingWord 30 - ኢየሱስ አምስት ሺህ ሰዎችን መገበ

Garis besar: Matthew 14:13-21; Mark 6:31-44; Luke 9:10-17; John 6:5-15

Nomor naskah: 1230

Bahasa: Amharic

Pengunjung: General

Jenis: Bible Stories & Teac

Tujuan: Evangelism; Teaching

Kutipan Alkitab: Paraphrase

Status: Approved

Naskah ini adalah petunjuk dasar untuk menerjemahkan dan merekam ke dalam bahasa-bahasa lain. Naskah ini harus disesuaikan seperlunya agar dapat dimengerti dan sesuai bagi setiap budaya dan bahasa yang berbeda. Beberapa istilah dan konsep yang digunakan mungkin butuh penjelasan lebih jauh, atau diganti atau bahkan dihilangkan.

Isi Naskah

ኢየሱስ በተለያዩ ብዙ መንደሮች እንዲሰብኩና ሰዎችን እንዲያስተምሩ ሐዋርያቱን ላከ። እነርሱ ኢየሱስ ወደ ነበረበት በተመለሱጊዜ፣ ያደረጉትንነገር ነገሩት።ከዚያ በኋላ ኢየሱስ ሐይቁን ተሻግረውጸጥታ ወዳለበት ቦታ አብረውት እንዲሄዱናጥቂት እንዲያርፉ ጋበዛቸው። ስለዚህጀልባ ውስጥ ገቡና ሐይቁን ተሻገሩ።

ነገር ግን በጀልባውሲሄዱ ኢየሱስንና ደቀ መዛሙርቱን ያዩአቸው ብዙሰዎች ነበሩ። እነዚህሰዎች ሊቀድሙአቸው በባሕሩዳርቻ ሮጡ። ስለዚህ ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ ወደ ማዶ በደረሱጊዜ፣ በጣም ብዙሰዎች አስቀድመውበዚያ ተገኝተው ይጠባበቁአቸው ነበር።

ሕዝቡ ሴቶችና ልጆች ሳይቈጠሩ ከ5000 በላይ ወንዶች ነበሩ። ኢየሱስ ለሕዝቡ እጅግ አዘነላቸው። ለኢየሱስ እነዚህ ሕዝብ እረኛ እንደሌላቸው በጎች ነበሩ። ስለዚህ አስተማራቸውና በመካከላቸው የነበሩትን በሽተኞች ፈወሳቸው።

በዚያ ምሽት ደቀ መዛሙርቱ እንዲህ ብለው ነገሩት፣ “ጊዜው መሽቶአልና በአቅራቢያው ከተሞች የሉም። የሚበሉትን ነገር ይገዙ ዘንድ ሕዝቡን አሰናብታቸው።”

ኢየሱስ ግን ደቀ መዛሙርቱን፣ “የሚበሉትን እናንተ ስጡአቸው!” አላቸው። እነርሱም፣“ይህን ማድረግ እንዴት እንችላለን? ያለን አምስት እንጀራናሁለት ዓሣ ብቻ ነው”ብለው መለሱለት።

ሃምሳ ሃምሳ ሆነው ሣሩ ላይ እንዲቀመጡ ለሕዝቡ ይነግሩ ዘንድ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ነገራቸው።

ከዚያም ኢየሱስ አምስቱን እንጀራና ሁለቱን ዓሣ ይዞ ወደ ሰማይ ተመለከተ፣ ስለ ምግቡም እግዚአብሔርን አመሰገነ።

ከዚያም ኢየሱስ እንጀራውንና ዓሣውን ቈረሰ። ለሕዝቡ እንዲያቀርቡም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጣቸው። ደቀ መዛሙርቱ ምግቡን ማደላቸውን ቀጠሉ፣ ከቶም አላለቀም! ሕዝቡ ሁሉ በልተው ጠገቡ።

ከዚያ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ቊርስራሹን ምግብ ሰበሰቡ፣ እርሱም ዐሥራ ሁለት መሶብ ሙሉ ነበር! ምግቡ ሁሉ የመጣው ከአምስቱ እንጀራና ከሁለቱ ዓሣ ነበር።

Keterangan terkait

Firman Kehidupan - GRN mempunyai rekaman pesan Injil dalam ribuan bahasa berisikan pesan berdasarkan Alkitab tentang keselamatan dan kehidupan Kristiani.

Unduhan-Unduhan Gratis - Disini anda dapat menemukan semua pesan naskah GRN yang utama dalam beberapa bahasa, ditambah gambar dan materi terkait lainnya yang dapat diunduh.

Perpustakaan Audio GRN - Bahan pengabaran Injil dan pengajaran dasar Alkitab yang sesuai dengan kebutuhan masyarakat dan budaya dalam berbagai macam bentuk dan format.

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?