unfoldingWord 12 - የእስራኤላውያን ከግብፅ መውጣት

unfoldingWord 12 - የእስራኤላውያን ከግብፅ መውጣት

Garis besar: Exodus 12:33-15:21

Nomor naskah: 1212

Bahasa: Amharic

Pengunjung: General

Jenis: Bible Stories & Teac

Tujuan: Evangelism; Teaching

Kutipan Alkitab: Paraphrase

Status: Approved

Naskah ini adalah petunjuk dasar untuk menerjemahkan dan merekam ke dalam bahasa-bahasa lain. Naskah ini harus disesuaikan seperlunya agar dapat dimengerti dan sesuai bagi setiap budaya dan bahasa yang berbeda. Beberapa istilah dan konsep yang digunakan mungkin butuh penjelasan lebih jauh, atau diganti atau bahkan dihilangkan.

Isi Naskah

እስራኤላውያን ከግብፅ በመውጣታቸው በጣም ደስ አላቸው። ከእንግዲህ ባሪያዎች አይደሉም፣ ወደ ተስፋዪቱ ምድርም በመጓዝ ላይ ነበሩ! ግብፃውያን ለእስራኤላውያን ወርቅና ብር ሌሎችም የከበሩ ነገሮች ሳይቀሩ የጠየቁትን ማንኛውንም ነገር ሰጡአቸውና ከግብፅ ሲወጡ ከሌሎች ብሔሮች የሆኑ አንዳንድ ሰዎች በእግዚአብሔር አምነው ከእስራኤላውያን ጋር ሄዱ።

እግዚአብሔር በፊታቸው በሚሄድ ቀን ረጅም በሆነ የደመና ዓምድ፣ ማታም ረጅም በሆነ የእሳት ዓምድ መራቸው። እግዚአብሔር ሁልጊዜ ከእነርሱ ጋር ነበርና ሲጓዙ መራቸው። ማድረግ ያለባቸው ነገር ቢኖር እርሱን መከተል ብቻ ነበር።

ከጥቂት ጊዜ በኋላ፣ ፈርዖንና ሕዝቡ ዐሳባቸውን ለወጡና እስራኤላውያን እንደ ገና የእነርሱ ባሪያዎች እንዲሆኑ ፈለጉ። እግዚአብሔር ብቸኛው እውነተኛ አምላክ መሆኑን ሕዝቡ እንዲያዩ፣ እንዲሁም እርሱ፣ ያሕዌ፣ ከፈርዖንና ከአማልክቱ የበለጠ ኃያል እንደ ሆነ ይረዱ ዘንድ ፈርዖንን ዐሳበ ግትር አደረገው።

ስለዚህ ፈርዖንና ጦር ሠራዊቱ እንደ ገና ባሪያዎቻቸው ሊያደርጉአቸው እስራኤላውያንን አሳደዱአቸው። እስራኤላውያን የግብፅ ጦር ሠራዊት ሲመጣ ባዩ ጊዜ፣ በፈርዖን ጦር ሠራዊትና በቀይ ባሕር መካከል እንደ ተጠመዱ ዐወቁ። በጣም ፈርተው ስለ ነበር፣ “ከግብፅ ለምን ወጣን? መሞታችን ነው!” ብለው ጮኹ።

ሙሴ እስራኤላውያንን፣ “አትፍሩ! ዛሬ እግዚአብሔር ይዋጋላችሁና ያድናችኋል” ብሎ ነገራቸው። ከዚያም እግዚአብሔር፣ “ወደ ቀይ ባሕር እንዲንቀሳቀሱ ለሕዝቡ ንገራቸው” ብሎ ለሙሴ ነገረው። ከዚያም እግዚአብሔር ግብፃውያን እስራኤላውያንን ማየት እንዳይችሉ የደመናውን ዓምድ በእስራኤላውያንና በግብፃውያን መካከል አደረገው።

እግዚአብሔር ለሙሴ በባሕሩ ላይ እጁን እንዲዘረጋና ውሃውን እንዲከፍለው ነገረው። ከዚያም እግዚአብሔር በባሕሩ መተላለፊያ መንገድ ይኖር ዘንድ ውሃውን ነፋስ ወደ ግራና ወደ ቀኝ እንዲያንቀሳቅሰው አደረገ።

እግዚአብሔር ለሙሴ በባሕሩ ላይ እጁን እንዲዘረጋና ውሃውን እንዲከፍለው ነገረው። ከዚያም እግዚአብሔር በባሕሩ መተላለፊያ መንገድ ይኖር ዘንድ ውሃውን ነፋስ ወደ ግራና ወደ ቀኝ እንዲያንቀሳቅሰው አደረገ።

እስራኤላውያን ውሃው በግራና በቀኛቸው ግድግዳ ሆኖላቸው በባሕሩ በደረቅ መሬት ላይ ተጓዙ።

ከዚያም እግዚአብሔር ግብፃውያኑ እስራኤላውያን ማምለጣቸውን ያዩ ዘንድ ደመናውን ከመንገዱ ወደ ላይ አንቀሳቀሰው። ግብፃውያን ከኋላቸው ሆነው ሊያሳድዱአቸው ወሰኑ።

ስለዚህ በባሕሩ መንገድ እስራኤላውያንን ተከተሉአቸው፣ ነገር ግን እግዚአብሔር ግብፃውያን እንዲጨነቁና ሰረገሎቻቸውም እንዲታሰሩ አደረገ። “ሽሹ! እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን እየተዋጋላቸው ነው!” ብለው ጮኹ።

እስራኤላውያን ባሕሩን በደኅና ከተሻገሩ በኋላ፣ እግዚአብሔር እንደ ገና እጁን እንዲዘረጋ ለሙሴ ነገረው። እርሱም በታዘዘ ጊዜ፣ ውሃው በግብፃውያን ሠራዊት ላይ ተመለሰና እንደ መጀመሪያው ሆነ። መላው የግብፃውያን ጦር ሠራዊት ሰጠመ።

እስራኤላውያን ግብፃውያን እንደ ሞቱ ባዩ ጊዜ በእግዚአብሔር አመኑ ሙሴም የእግዚአብሔር ነቢይ መሆኑን አመኑ።

ደግሞም እስራኤላውያን እግዚአብሔር ከሞትና ከባርነት ስለ አዳናቸው በብዙ ደስታ ደስ አላቸው! አሁን እግዚአብሔርን ለማገልገል ነጻ ሆኑ። እስራኤላውያን እርሱ ከግብፃውያን ጦር ሠራዊት ስለ አዳናቸው ዐዲሱን ነጻነታቸውን ለማክበርና እግዚአብሔርን ለማመስገን ብዙ መዝሙሮችን ዘመሩ።

እንዴት እግዚአብሔር በግብፃውያን ላይ ድልን እንደ ሰጣቸውና ባሪያዎች ከመሆን እንዳዳናቸው ያስታውሱ ዘንድ በያመቱ ፋሲካን እንዲያከብሩ እስራኤላውያንን አዘዛቸው። ፍጹም የሆነ ጠቦት አርደው ካልቦካ ቂጣ ጋር በመብላት ተደሰቱ።

Keterangan terkait

Firman Kehidupan - GRN mempunyai rekaman pesan Injil dalam ribuan bahasa berisikan pesan berdasarkan Alkitab tentang keselamatan dan kehidupan Kristiani.

Unduhan-Unduhan Gratis - Disini anda dapat menemukan semua pesan naskah GRN yang utama dalam beberapa bahasa, ditambah gambar dan materi terkait lainnya yang dapat diunduh.

Perpustakaan Audio GRN - Bahan pengabaran Injil dan pengajaran dasar Alkitab yang sesuai dengan kebutuhan masyarakat dan budaya dalam berbagai macam bentuk dan format.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons