unfoldingWord 35 - የርኅሩኁ አባት ታሪክ

unfoldingWord 35 - የርኅሩኁ አባት ታሪክ

Garis besar: Luke 15

Nomor naskah: 1235

Bahasa: Amharic

Pengunjung: General

Jenis: Bible Stories & Teac

Tujuan: Evangelism; Teaching

Kutipan Alkitab: Paraphrase

Status: Approved

Naskah ini adalah petunjuk dasar untuk menerjemahkan dan merekam ke dalam bahasa-bahasa lain. Naskah ini harus disesuaikan seperlunya agar dapat dimengerti dan sesuai bagi setiap budaya dan bahasa yang berbeda. Beberapa istilah dan konsep yang digunakan mungkin butuh penjelasan lebih jauh, atau diganti atau bahkan dihilangkan.

Isi Naskah

አንድ ቀን ኢየሱስ ብዙ ቀረጥ ሰብሳቢዎችንና ሊሰሙት የተሰበሰቡ ሌሎች ኃጢአተኞችን ያስተምር ነበር።

ደግሞም በዚያ የነበሩ አንዳንድ የሃይማኖት መሪዎች ኢየሱስ ኃጢአተኞችን ወዳጆች አድርጎ ሲቀበላቸው ዐዩ፣ እርስ በርሳቸውም ይነቅፉት ጀመር። ስለዚህ ኢየሱስ ይህንን ታሪክ ነገራቸው።

ሁለት ልጆች ያሉት አንድ ሰው ነበር። ታናሹ ልጅ አባቱን፣ አባቴ ሆይ፣ ከገንዘብህ የሚደርሰኝን ክፍል አሁን ስጠኝ!’ አለው። ስለዚህ አባትዬው ገንዘቡን ለሁለቱ ልጆቹ አካፈላቸው።"

“ታናሹ ልጅ ወዲያውኑ ያለውን ሁሉ ሰበሰበና ሩቅ አገር ሄዶ በኃጢአት እየኖረ ገንዘቡን አጠፋ።

“ከዚያ በኋላ ታናሹ ልጅ በነበረበት አገር ጽኑ ረሀብ ሆነ፣ ምግብ የሚገዛበት ገንዘብም አልነበረውም። ስለዚህ ብቸኛ የነበረውን፣ እሪያዎችን የመመገብ ሥራ ያዘ። በጣም ተጐሳቊሎና ተርቦ ስለ ነበር የእሪያዎችን ምግብ ለመብላት ይመኝ ነበር።”

“በመጨረሻ፣ ታናሹ ልጅ ለራሱ እንዲህ አለ፣ ‘ምን እያደረግሁ ነው? የአባቴ አገልጋዮች ሁሉ የሚበሉት ብዙ ምግብ አላቸው፣ እኔ ግን ተርቤአለሁ። ወደ አባቴ ተመልሾ እሄድና ከአገልጋዮቹ አንዱ እንዲያደርገኝ እለምነዋለሁ።’”

ስለዚህ ታናሹ ልጅ ወደ አባቱ ቤት መመለስ ጀመረ። ገና በሩቅ እያለ አባቱ ዐየውና አዘነለት። ወደ ልጁ ሮጠና አቀፈው ሳመውም።"

“ልጁም አለ፣ ‘አባቴ ሆይ፣ እግዚአብሔርንና አንተን በድዬአለሁ። ልጅህ ልባል አይገባም።’”

“ነገር ግን አባቱ ከአገልጋዮቹ ለአንዱ እንዲህ ብሎ ነገረው፣ ‘ፈጥነህ ሂድና ማለፊያ ልብስ አምጥተህ ለልጄ አልብሰው! ለጣቱ ቀለበት ለእግሩም ጫማ አድርግለት። ከዚያም እንበላና ደስ ይለን ዘንድ የሰባ ፍሪዳ አምጥታችሁ እረዱ፣ ምክንያቱም ይህ ልጄ ሞቶ ነበር፣ ሕያውም ሆኖአል! ጠፍቶ ነበር፣ አሁን ግን ተገኝቶአል!’”

“ስለዚህ ሰዎቹ ደስ ይላቸው ጀመር። ብዙ ሳይቆይ፣ ይሠራበት ከነበረው እርሻ ታላቅ ወንድሙ ወደ ቤት መጣ። የሙዚቃና የዘፈን ድምፅ ሰማ፣ ምን እየሆነ ነው ብሎም ተገረመ።”

“ታላቁ ልጅ ወንድሙ ስለ መጣ እየተደሰቱ መሆናቸውን ባወቀ ጊዜ፣ በጣም ስለ ተቈጣ ወደ ቤት ለመግባት ፈቃደኛ አልሆነም። አባቱ ወጣና ገብቶ ከእነርሱ ጋር እንዲደሰት ለመነው፣ እርሱ ግን እምቢ አለ።”

ታላቁ ልጅ አባቱን እንዲህ አለው፣ ‘በእነዚህ ዓመታት ሁሉ በታማኝነት ለአንተ ሠርቼአለሁ! ከቶ ትእዛዝህን አልተላለፍኩም፣ እስካሁንም ከጓደኞቼ ጋር እንድደሰት አንድ ጥቦት ፍየል እንኳ አልሰጠኸኝም። ኃጢአት በመሥራት ገንዘብህን ያጠፋው ይህ ልጅህ ግን ወደ ቤት በመጣ ጊዜ፣ የሰባ ፍሪዳ አረድህለት!"

“አባቱ እንዲህ ብሎ መለሰለት፣ ‘ልጄ፣ አንተ ሁልጊዜ ከእኔ ጋር ነህ፣ ያለኝም ነገር ሁሉ የአንተ ነው። መደሰታችን ግን ትክክል ነው፣ ምክንያቱም ወንድምህ ሞቶ ነበር፣ አሁን ግን ሕያው ሆኖአል። ጠፍቶ ነበር፣ አሁን ግን ተገኝቶአል!”

Keterangan terkait

Firman Kehidupan - GRN mempunyai rekaman pesan Injil dalam ribuan bahasa berisikan pesan berdasarkan Alkitab tentang keselamatan dan kehidupan Kristiani.

Unduhan-Unduhan Gratis - Disini anda dapat menemukan semua pesan naskah GRN yang utama dalam beberapa bahasa, ditambah gambar dan materi terkait lainnya yang dapat diunduh.

Perpustakaan Audio GRN - Bahan pengabaran Injil dan pengajaran dasar Alkitab yang sesuai dengan kebutuhan masyarakat dan budaya dalam berbagai macam bentuk dan format.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons