unfoldingWord 41 - እግዚአብሔር ኢየሱስን ከሙታን አስነሣው
![unfoldingWord 41 - እግዚአብሔር ኢየሱስን ከሙታን አስነሣው](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_28_04.jpg)
Grandes lignes: Matthew 27:62-28:15; Mark 16:1-11; Luke 24:1-12; John 20:1-18
Numéro de texte: 1241
Lieu: Amharic
Audience: General
Objectif: Evangelism; Teaching
Features: Bible Stories; Paraphrase Scripture
Statut: Approved
Les scripts sont des directives de base pour la traduction et l'enregistrement dans d'autres langues. Ils doivent être adaptés si nécessaire afin de les rendre compréhensibles et pertinents pour chaque culture et langue différente. Certains termes et concepts utilisés peuvent nécessiter plus d'explications ou même être remplacés ou complètement omis.
Corps du texte
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_27_21.jpg)
ወታደሮቹ ኢየሱስን ከሰቀሉት በኋላ፣ የማያምኑት የአይሁድ መሪዎች ጲላጦስን፣ “ያ ውሸታም፣ ኢየሱስ፣ ከሦስት ቀን በኋላ ከሙታን እነሣለሁ ብሎአል። ደቀ መዛሙርቱ ሥጋውን እንዳይሰርቁትና ከሙታን ተነሣ እንዳይሉ ለማረጋገጥ አንድ ሰው መቃብሩን መጠበቅ አለበት” አሉት።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_27_22.jpg)
ጲላጦስ፣ “አንዳንድ ወታደሮችን ውሰዱና መቃብሩን በተቻለ መጠን እንዲጠበቅ አድርጉ” አለ። ስለዚህ በመቃብሩ መግቢያ ባለው ድንጋይ ላይ ማኅተም አደረጉና ሥጋውን ማንም እንዳይሰርቀው ለማረጋገጥ በዚያ ወታደሮችን አቆሙ።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_28_01.jpg)
ኢየሱስ ከተሰቀለ በኋላ የነበረ ቀን ሰንበት ነበረ። አይሁድ በዚያ ቀን ወደ መቃብር እንዲሄዱ አይፈቀድላቸውም ነበር። ስለዚህ ከሰንበት ቀን በኋላ በማለዳ ብዙ ሴቶች ሥጋው ላይ ተጨማሪ ሽቱ ለማርከፍከፍ ወደ ኢየሱስ መቃብር ሊሄዱ ተዘጋጁ።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_28_02.jpg)
በድንገትም ታላቅ የምድር መንቀጥቀጥ ሆነ። እንደ መብረቅ የሚያበራ መልአክ ከሰማይ ታየ። የመቃብሩን መግቢያ ከድኖ የነበረውን ድንጋይ አንከባለለና ተቀመጠበት። መቃብሩን ይጠብቁ የነበሩት ወታደሮች ፈሩና እንደ ሞቱ ሰዎች ሆነው መሬት ላይ ወደቁ።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_28_04.jpg)
ሴቶቹ ወደ መቃብሩ በደረሱ ጊዜ መልአኩ፣ “አትፍሩ ኢየሱስ እዚህ የለም። ልክ እነሣለሁ ብሎ እንደ ተናገረው ከሙታን ተነሥቶአል! መቃብሩን ተመልከቱና እዩ” ብሎ ነገራቸው። ሴቶቹ ወደ መቃብሩ ውስጥ ተመለከቱና የኢየሱስን ሥጋ ያኖሩበትን ስፍራ ዐዩ። ሥጋው በዚያ አልነበረም!
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_28_05.jpg)
ከዚያም መልአኩ ለሴቶቹ፣ “ሂዱና ‘ኢየሱስ ከሙታን ተነሥቶአል ቀድሞአችሁ ወደ ገሊላ ይሄዳል ብላችሁ ለደቀ መዛሙርቱ ንገሩአቸው’” ብሎ ነገራቸው።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z40_Mt_28_06.jpg)
ሴቶቹ በፍርሃትና በታላቅ ደስታ ተሞልተው ነበር። የምሥራቹን ለደቀ መዛሙርቱ ለመንገር እየሮጡ ሄዱ።
![](https://static.globalrecordings.net/300x200/z42_Lk_24_07.jpg)
ሴቶቹ የምሥራቹን ለደቀ መዛሙርቱ ለመንገር በመሄድ ላይ እያሉ፣ ኢየሱስ ታያቸው፣ እነርሱም ሰገዱለት። ኢየሱስ፣ “አትፍሩ። ወደ ገሊላ እንዲሄዱ ለደቀ መዛሙርቴ ንገሩአቸው። በዚያ ያዩኛል” አላቸው።