unfoldingWord 10 - ዐሥሩ መቅሠፍቶች

unfoldingWord 10 - ዐሥሩ መቅሠፍቶች

Outline: Exodus 5-10

Script Number: 1210

Language: Amharic

Audience: General

Genre: Bible Stories & Teac

Purpose: Evangelism; Teaching

Bible Quotation: Paraphrase

Status: Approved

Scripts are basic guidelines for translation and recording into other languages. They should be adapted as necessary to make them understandable and relevant for each different culture and language. Some terms and concepts used may need more explanation or even be replaced or omitted completely.

Script Text

ሙሴና አሮን ወደ ፈርዖን ሄዱ። “የእስራኤል አምላክ ‘ሕዝቤንልቀቅ !’” ይላሃል አሉት። ፈርዖን አልሰማቸውም። እስራኤላውያን ነጻ ሆነው እንዲሄዱ በማድረግፈንታ ከዚህም የከበደ ሥራ እንዲሠሩ አስገደዳቸው!

ፈርዖን ሕዝቡን አልለቅም ማለቱን ቀጠለ፣ ስለዚህ እግዚአብሔር በግብፅ ላይ ዐሥር መቅሠፍቶችን ላከ። እግዚአብሔር በእነዚህ መቅሠፍቶች በኩል ከፈርዖንና ከግብፅ አማልክት ሁሉ ይልቅ ኃያል መሆኑን ለፈርዖን ዐሳየው።

እግዚአብሔር የዓባይን ውሃ ወደ ደም ለወጠው፣ ነገር ግን ፈርዖን አሁንም እስራኤላውያንን አልለቀቃቸውም።

እግዚአብሔር በግብፅ ሁሉ ላይ እንቁራሪቶችን ላከ። ፈርዖን ሙሴን እንቁራሪቶቹን እንዲያርቅ ለመነው። ሆነም ቀረ ግን እንቁራሪቶቹ ሁሉ ሞቱ። ፈርዖን ልቡን አደነደነና እስራኤላውያንን ከግብፅ እንዲወጡ አልለቀቃቸውም።

ስለዚህ እግዚአብሔር ትንኞችን ላከ። ከዚያም ዝንቦችን ላከ። ፈርዖን ሙሴንና አሮንን ጠራና መቅሠፍቱን ካቆሙ እስራኤላውያን ከግብፅ መሄድ እንደሚችሉ ነገራቸው። ሙሴ በጸለየ ጊዜ እግዚአብሔር ዝንቦችን ሁሉ ከግብፅ አስወገደ። ነገር ግን ፈርዖን ልቡን አደነደነና ሕዝቡን አልለቀቀም።

ቀጥሎ እግዚአብሔር የግብፃውያን ከብቶች ሁሉ ታመው እንዲሞቱ አደረገ። ነገር ግን የፈርዖን ልብ ደነደነና እስራኤላውያንን አልለቀቀም።

ከዚያም እግዚአብሔር በፈርዖን ፊት ዐመድ ወደ ሰማይ እንዲበትን ለሙሴ ነገረው። ዐመዱን በበተነ ጊዜ በግብፃውያን ላይ የሚያም ቊስል ሆነ፣ በእስራኤላውያን ላይ ግን ቊስሉ አልሆነባቸውም። እግዚአብሔር የፈርዖንን ልብ አደነደነ፣ ፈርዖንም እስራኤላውያንን አልለቀቀም።

ከዚያ በኋላ እግዚአብሔር በግብፅ ያለውን አብዛኛውን ቡቃያ ያጠፋና ከቤት ውጪ የነበረውን ማንኛውንም ሰው የገደለ በረዶ ላከ። ፈርዖን ሙሴንና አሮንን ጠርቶ፣ “በድዬአለሁ። መሄድ ትችላላችሁ” ብሎ ነገራቸው። ስለዚህ ሙሴ ጸለየ፣ በረዶውም ከሰማይ መዝነቡን አቆመ።

ነገር ግን ፈርዖን እንደ ገና ኃጢአት ሠራ ልቡንም አደነደነ። እስራኤላውያንን አልለቀቀም።

ስለዚህ እግዚአብሔር በግብፅ ላይ የአንበጣዎችን መንጋ አመጣ። እነዚህ አንበጣዎች በረዶው ያላጠፋውን ሰብል ሁሉ በሉት።

ከዚያም እግዚአብሔር ለሦስት ቀን የቆየ ጨለማ ላከ። ግብፃውያን ከቤቶቻቸው እስከማይወጡ ድረስ በጣም ጨልሞ ነበር። እስራኤላውያን በሚኖሩበት ስፍራ ግን ብርሃን ነበረ።

ከእነዚህ ዘጠኝ መቅሠፍቶች በኋላ እንኳ ፈርዖን አሁንም እስራኤላውያንን አልለቅም አለ። ፈርዖን ስለማይሰማ፣ እግዚአብሔር አንድ የመጨረሻ መቅሠፍት ለመላከ ወሰነ። ይህ የፈርዖንን ዐሳብ ይለውጣል።

Related information

Words of Life - Audio gospel messages in thousands of languages containing Bible based messages about salvation and Christian living.

Free downloads - Here you can find all the main GRN message scripts in several languages, plus pictures and other related materials, available for download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons