unfoldingWord 37 - ኢየሱስ አልዓዛርን ከሞት አስነሣ

Zusammenfassung: John 11:1-46

Skript Nummer: 1237

Sprache: Amharic

Zuschauer: General

Genre: Bible Stories & Teac

Zweck: Evangelism; Teaching

Bibelzitat: Paraphrase

Status: Approved

Skripte dienen als grundlegende Richtlinie für die Übersetzung und Aufnahme in anderen Sprachen. Sie sollten, soweit erforderlich, angepasst werden, um sie für die jeweilige Kultur und Sprache verständlich und relevant zu machen. Einige der verwendeten Begriffe und Konzepte müssen unter Umständen ausführlicher erklärt oder sogar ersetzt oder ganz entfernt werden.

Skript Text

አንድ ቀን ኢየሱስ አልዓዛር በጣም ታሞአል የሚል መልእክት ደረሰው። አልዓዛርና ሁለቱ እኅቶቹ ማርያምና ማርታ የኢየሱስ የቅርብ ወዳጆች ነበሩ። ኢየሱስ ይህንን ወሬ በሰማ ጊዜ፣ “ይህ ሕመም ለእግዚአብሔር ክብር ነው እንጂ ለሞት አይደለም” አለ። ኢየሱስ ወዳጆቹን ይወዳቸው ነበር፣ ነገር ግን ለሁለት ቀናት በነበረበት ስፍራ ቆየ።

ሁለቱ ቀናት ካለፉ በኋላ፣ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን፣ “ወደ ይሁዳ እንሂድ” አላቸው። “ነገር ግን መምህር ሆይ፣”ልክ ከጥቂት ጊዜ በፊት በዚያ ያሉት ሕዝብ ሊገድሉህ ይፈልጉ ነበር!" ብለው ደቀ መዛሙርቱ መለሱለት። ኢየሱስ፣ “ወዳጃችን አልዓዛር አንቀላፍቶአል፣ ከእንቅልፉ ላስነሣው እሄዳለሁ” አላቸው።

የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት፣ “ጌታ ሆይ፣ አልዓዛር ተኝቶስ ከሆነ፣ ይድናል” ብለው መለሱለት። በዚያን ጊዜ ኢየሱስ በግልጽ ነገራቸው፣ “አልዓዛር ሞቶአል። እናንተ በእኔ ታምኑ ዘንድ እዚያ ባለመኖሬ ደስ ብሎኛል።”

ኢየሱስ አልዓዛር ወደ ተወለደበት ከተማ በደረሰ ጊዜ፣ አልዓዛር ከሞተ አራት ቀን ሆኖት ነበር። ማርታ ኢየሱስን ልትገናኘው ወጣችና እንዲህ አለች፣ “ጌታ ሆይ፣ አንተ እዚህ ብትኖር ኖሮ ወንድሜ አይሞትም ነበር። ነገር ግን እግዚአብሔር የምትለምነውን ሁሉ እንደሚሰጥህ አምናለሁ።”

ኢየሱስ እንዲህ ብሎ መለሰላት፣ “እኔ ትንሣኤና ሕይወት ነኝ። በእኔ የሚያምን ሁሉ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል። በእኔ የሚያምን ሁሉ ከቶ አይሞትም። ይህን ታምኛለሽን? ማርታ፣”አዎን፣ ጌታ ሆይ! አንተ መሲሑ፣ የእግዚአብሔር ልጅ መሆንህን አምናለሁ" ብላ መለሰችለት።

ከዚያም ማርያም መጣች። በኢየሱስ እግር ወደቀችና፣ “ጌታ ሆይ፣ አንተ በዚህ ኖረህ ብትሆን ኖሮ ወንድሜ ባልሞተም ነበር” አለች። ኢየሱስ፣ “አልዓዛርን ወዴት ነው ያኖራችሁት?” ብሎ ጠየቃቸው። “በመቃብር ነው። ናና እይ” ብለው ነገሩት። ከዚያም ኢየሱስ አለቀሰ።

መቃብሩ ዋሻ ነበር፣ ድንጋይም ተገጥሞበት ነበር። ኢየሱስ ወደ መቃብሩ በደረሰ ጊዜ ድንጋዩን አንከባሉት" ብሎ ነገራቸው። ነገር ግን ማርታ፣ “ከሞተ አራት ቀን ሆኖታል። አሁን ይሸታል” አለችው።

ኢየሱስ፣ “በእኔ ብታምኚስ የእግዚአብሔርን ክብር እንድታዪ አልነገርኩሽምን?” አላት። ስለዚህ ድንጋዩን አንከባለሉት።

ከዚያ በኋላ ኢየሱስ ወደ ላይ ተመለከተና፣ “አባት ሆይ፣ ስለምትሰማኝ አመሰግንሃለሁ። አንተ ሁልጊዜ እንደምትሰማኝ ዐውቃለሁ፣ ነገር ግን አንተ እንደ ላክኸኝ ያምኑ ዘንድ እዚህ ስለ ቆሙት ስለ እነዚህ ሰዎች ሁሉ ይህን እላለሁ” አለ። ከዚያም ኢየሱስ፣ “አልዓዛር ሆይ፣ ወደ ውጭ ና!” ብሎ ጮኸ።

ስለዚህ አልዓዛር ወጣ! በከፈን እንደ ተገነዘ ነበር። ኢየሱስም፣ “ፍቱትና ይሂድ ተዉት!” አላቸው። ከአይሁድ ብዙዎች በዚህ ተአምር ምክንያት በኢየሱስ አመኑ።

ነገር ግን የአይሁድ የሃይማኖት መሪዎች ቀኑ፣ ስለዚህ ኢየሱስንና አልዓዛርን እንዴት መግደል እንዳለባቸው ለማቀድ በአንድ ላይ ተሰበሰቡ።

Verwandte Informationen

Worte des Lebens - GRN hat Audio-Gospel-Botschaften in tausenden von Sprachen, beinhaltet bibelbasierte Botschaften über die Erettung und das christliche Leben.

Freie Downloads - Hier findet man alle GRN Botschaften, Schriften in vielen Sprachen, plus Bilder und andere verwandte Materialien, verfügbar zum Download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the right audio or video format - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?