unfoldingWord 29 - የምሕረት የለሹ ባሪያ ታሪክ

unfoldingWord 29 - የምሕረት የለሹ ባሪያ ታሪክ

Zusammenfassung: Matthew 18:21-35

Skript Nummer: 1229

Sprache: Amharic

Zuschauer: General

Genre: Bible Stories & Teac

Zweck: Evangelism; Teaching

Bibelzitat: Paraphrase

Status: Approved

Skripte dienen als grundlegende Richtlinie für die Übersetzung und Aufnahme in anderen Sprachen. Sie sollten, soweit erforderlich, angepasst werden, um sie für die jeweilige Kultur und Sprache verständlich und relevant zu machen. Einige der verwendeten Begriffe und Konzepte müssen unter Umständen ausführlicher erklärt oder sogar ersetzt oder ganz entfernt werden.

Skript Text

አንድ ቀን ጴጥሮስ ኢየሱስን፣ “መምህር ሆይ፣ ወንድሜ ቢበድለኝ ስንት ጊዜ ይቅር ልበለው? እስከ ሰባት ጊዜ ነውን?” ብሎ ጠየቀው። ኢየሱስ፣ “ሰባት ጊዜ አይደለም፣ ሰባ ጊዜ ሰባት እንጂ” አለው። ኢየሱስ ይህን ሲል ሁልጊዜ ይቅር ማለት አለብን ማለቱ ነው። ከዚያም ኢየሱስ ይህን ታሪክ ተናገረ።

ኢየሱስ እንዲህ አለ፣ “የእግዚአብሔር መንግሥት ባሮቹን ሊቈጣጠር የፈለገን ንጉሥ ትመስላለች። ከባሮቹ አንዱ የ10,000 መክሊት የሚያክል ከፍተኛ ዕዳ ነበረበት።”

ባሪያው ዕዳን መክፈል ስላልቻለ፣ ንጉሡ፣ “ዕዳውን ይከፍል ዘንድ ይህን ሰውና ቤተ ሰቡን ሽጡአቸው” አለው።

“ባሪያው በንጉሡ ፊት በጉልበቱ ወደቀና፣ ‘እባክህን ታገሠኝ፣ ያለብኝን ዕዳ ሁሉ እከፍልሃለሁ’ አለው። ንጉሡ ለባሪያው አዘነለት፣ ዕዳውንም ሁሉ ሰረዘለትና እንዲሄድ ለቀቀው።”

“ነገር ግን ባሪያው ከንጉሡ ዘንድ በወጣ ጊዜ፣ የአራት ወር ደመወዝ የሚሆን ዕዳ ያለበትን ባልንጀሮቹ ከሆኑት ባሪያዎች አንዱን አገኘ። ባሪያው ባልንጀራው የሆነውን ባሪያ ያዘውና፣ ‘ዕዳህን ክፈለኝ!’” አለው።

“ባልንጀራው ባሪያ በጉልበቱ ወድቆ፣ ‘እባክህን ታገሠኝ፣ ያለብኝን ዕዳ ሁሉ እከፍልሃለሁ’ አለው። ነገር ግን በዚህ ፈንታ ያ ባሪያ ባልንጀራ ባሪያውን ዕዳውን እስኪከፍለው ድረስ በወኅኒ ጣለው።”

“ሌሎች ባሮችም የሆነውን ነገር ዐይተው እጅግ ተረበሹ። ወደ ንጉሡ ሄደውም የሆነውን ነገር ሁሉ ነገሩት።”

“ንጉሡ ባሪያውን ጠራና፣ ‘አንተ ክፉ ባሪያ! ስለ ለመንኸኝ ዕዳህን ተውሁልህ። አንተም ይህንኑ ማድረግ ይገባህ ነበር’ አለው። ንጉሡ በጣም ተቈጣና ዕዳውን ሁሉ እስኪከፍል ድረስ ክፉውን ባሪያ በወኅኒ ጣለው።”

ከዚያም ኢየሱስ እንዲህ አለ፣ “ከእናንተ እያንዳንዱ ወንድሙን ይቅር ካላለ፣ እንዲሁ ደግሞ የሰማይ አባቴ ያደርግባችኋል።”

Verwandte Informationen

Worte des Lebens - GRN hat Audio-Gospel-Botschaften in tausenden von Sprachen, beinhaltet bibelbasierte Botschaften über die Erettung und das christliche Leben.

Freie Downloads - Hier findet man alle GRN Botschaften, Schriften in vielen Sprachen, plus Bilder und andere verwandte Materialien, verfügbar zum Download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons