unfoldingWord 18 - የተከፈለው መንግሥት

unfoldingWord 18 - የተከፈለው መንግሥት

Esquema: 1 Kings 1-6; 11-12

Número de guió: 1218

Llenguatge: Amharic

Públic: General

Gènere: Bible Stories & Teac

Propòsit: Evangelism; Teaching

Citació bíblica: Paraphrase

Estat: Approved

Els scripts són pautes bàsiques per a la traducció i l'enregistrament a altres idiomes. S'han d'adaptar segons sigui necessari perquè siguin comprensibles i rellevants per a cada cultura i llengua diferents. Alguns termes i conceptes utilitzats poden necessitar més explicació o fins i tot substituir-se o ometre completament.

Text del guió

ከብዙ ዓመታት በኋላ፣ዳዊት ሞተ፣ ልጁ ሰሎሞንም በእስራኤል ላይይገዛ ጀመር። እግዚአብሔር ለሰሎሞን ተናገረውና በይበልጥ ምን እንደሚፈልግ ጠየቀው። ሰሎሞን ጥበብን በለመነጊዜ፣ በዓለም ላይእጅግ በጣም ጠቢብ ሰው አደረገው። ሰሎሞን ብዙ ነገሮችን ተማረናበጣም ጠቢብ ፈራጅ ሆነ። ደግሞም እግዚአብሔርበጣም ባለ ጠጋ አደረገው።

ሰሎሞን በኢየሩሳሌም አባቱ ዳዊት ያቀደውንና ለግንባታው የሚያስፈልጉ ነገሮች የሰበሰበለትን ቤተ መቅደሱን ሠራ። አሁን ሕዝቡ በመገናኛው ድንኳ ፈንታ በቤተ መቅደሱ እግዚአብሔርን አመለኩ መሥዋዕትንም አቀረቡለት። እግዚአብሔር መጥቶ በቤተ መቅደሱ ተገኘ፣ በዚያም ከሕዝቡ ጋር ኖረ።

ነገር ግን ሰሎሞን ከሌሎች አገሮች የሆኑ ሴቶችን ወደደ። ከሞላ ጐደል 1000 የሚሆኑ ብዙ ሴቶችን በማግባት ለእግዚአብሔር አልታዘዘም! ከእነዚህ ሴቶች ብዙዎቹ ከውጪ አገሮች መጡ፣ ጣዖቶቻቸውን አመጡና እነርሱኑ ማምለካቸውን ቀጠሉ። ሰሎሞን በሸመገለ ጊዜ፣ እርሱም ደግሞ የእነርሱን አማልክት አመለከ።

እግዚአብሔር በሰሎሞን ላይ ተቈጣ፣ ሰሎሞን ባለመታመኑ እንደ መቀጣጫ ሰሎሞን ከሞተ በኋላ የእስራኤልን ሕዝብ ወደ ሁለት መንግሥታት እንደሚከፍል ተናገረ።

ሰሎሞን ከሞተ በኋላ ልጁ ሮብዓም ነገሠ። ሮብዓም ሞኝ ነበረ። የእስራኤል ሕዝብ በሙሉ ንጉሥነቱን ሊያጸድቁለት ተሰብስበው መጡ። ሰሎሞን ብዙ ከባድ ሥራ እንዳሠራቸውና ብዙ ግብር እንዳስከፈላቸው ለሮብዓም ቅሬታቸውን ተናገሩ።

ሮብዓም በሞኝነት እንዲህ ብሎ መለሰላቸው፣ “አባቴ ሰሎሞን ከባድ ሥራ አሠርቶናል ብላችሁ ዐስባችኋል፣ ነገር ግን እኔ ከእርሱ የባሰ ከባድ ሥራ አሠራችኋለሁ፣ ከእርሱ የባሰም በኃይል እቀጣችኋለሁ።”

ዐሥሩ የእስራኤል ሕዝብ ነገዶች በሮብዓም ላይ ዓመፁ። ሁለት ነገዶች ብቻ ለእርሱ ባላቸው ታማኝነት ቀጠሉ። እነዚህ ሁለት ነገዶች የይሁዳ መንግሥት ሆኑ።

በሮብዓም ላይ ያመፁት ሌሎቹ ዐሥር የእስራኤል ሕዝብ ነገዶች ኢዮርብዓም የተባለውን ሰው ንጉሣቸው አድርገው ሾሙት። በምድሪቱ ሰሜናዊ ክፍል መንግሥታቸውን አቋቋሙ የእስራኤል መንግሥት ተብለውም ተጠሩ።

ኢዮርብዓም በእግዚአብሔር ላይ ዓመፀና ሕዝቡ ኃጢአት እንዲሠሩ አደረገ። በይሁዳ መንግሥት ባለው ቤተ መቅደስ እግዚአብሔርን በማምለክ ፈንታ ሕዝቡ ያመልኩአቸው ዘንድ ሁለት ጣዖታትን ሠራላቸው።

የይሁዳና የእስራኤል መንግሥታት ጠላቶች ሆኑና ብዙ ጊዜ እርስ በርስ ተዋጉ።

በዐዲሲቱ የእስራኤል መንግሥት፣ ነገሥታቱ ሁሉ ክፉዎች ነበሩ። ከእነዚህ ነገሥታት አብዛኞቹ፣ በእነርሱ ቦታ መንገሥ በፈለጉ ሌሎች እስራኤላውያን ተገደሉ።

ነገሥታቱ ሁሉና አብዛኞቹ የእስራኤል መንግሥት ሕዝብ ጣዖትን አመለኩ። የጣዖት አምልኮአቸው ብዙውን ጊዜ ግብረ ገብነት የጐደለው የግብረ ሥጋ ግንኙነትና አንዳንድ ጊዜ ልጆችን መሠዋትን ያካተተ ነበር።

የይሁዳ ነገሥታት የዳዊት ዝርያዎች ነበሩ። ከእነዚህ ነገሥታት አንዳንዶቹ በትክክል የገዙና እግዚአብሔርን ያመለኩ ጥሩ ሰዎች ነበሩ። ነገር ግን አብዛኞቹ ነገሥታት ክፉዎችና ብልሹዎች ነበሩ፣ ጣዖታትንም ያመልኩ ነበር። አንዳንዶቹ ነገሥታት ልጆቻቸውን እንኳ ለሐሰት አማልክት ሠውተዋል። ደግሞም አብዛኞቹ የይሁዳ ሕዝብ በእግዚአብሔር ላይ ዓመፁ ሌሎች አማልክትንም አመለኩ።

Informació relacionada

Free downloads - Here you can find all the main GRN message scripts in several languages, plus pictures and other related materials, available for download.

The GRN Audio Library - Evangelistic and basic Bible teaching material appropriate to the people's need and culture in a variety of styles and formats.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares it's audio, video and written scripts under Creative Commons